King James Version

Amharic: New Testament

1 Thessalonians

5

1But of the times and the seasons, brethren, ye have no need that I write unto you.
1ወንድሞች ሆይ፥ ስለ ዘመናትና ስለ ወራት ምንም እንዲጻፍላችሁ አያስፈልጋችሁም፤
2For yourselves know perfectly that the day of the Lord so cometh as a thief in the night.
2የጌታ ቀን፥ ሌባ በሌሊት እንደሚመጣ፥ እንዲሁ ይመጣ ዘንድ ራሳችሁ አጥብቃችሁ አውቃችኋልና።
3For when they shall say, Peace and safety; then sudden destruction cometh upon them, as travail upon a woman with child; and they shall not escape.
3ሰላምና ደኅንነት ነው ሲሉ ያን ጊዜ ምጥ እርጕዝን እንደሚይዛት ጥፋት በድንገት ይመጣባቸዋል ከቶም አያመልጡም።
4But ye, brethren, are not in darkness, that that day should overtake you as a thief.
4እናንተ ግን፥ ወንድሞች ሆይ፥ ቀኑ እንደ ሌባ ይደርስባችሁ ዘንድ በጨለማ አይደላችሁም፥
5Ye are all the children of light, and the children of the day: we are not of the night, nor of darkness.
5ሁላችሁ የብርሃን ልጆች የቀንም ልጆች ናችሁና። እኛ ከሌሊት ወይም ከጨለማ አይደለንም፤
6Therefore let us not sleep, as do others; but let us watch and be sober.
6እንግዲያስ እንንቃ በመጠንም እንኑር እንጂ እንደ ሌሎች አናንቀላፋ።
7For they that sleep sleep in the night; and they that be drunken are drunken in the night.
7የሚያንቀላፉ በሌሊት ያንቀላፋሉና፥ የሚሰክሩም በሌሊት ይሰክራሉና፤
8But let us, who are of the day, be sober, putting on the breastplate of faith and love; and for an helmet, the hope of salvation.
8እኛ ግን ከቀን ስለ ሆንን፥ የእምነትንና የፍቅርን ጥሩር የመዳንንም ተስፋ እንደ ራስ ቁር እየለበስን በመጠን እንኑር፤
9For God hath not appointed us to wrath, but to obtain salvation by our Lord Jesus Christ,
9እግዚአብሔር ለቍጣ አልመረጠንምና፥ በጌታችን በኢየሱስ ክርስቶስ መዳንን ለማግኘት ነው እንጂ።
10Who died for us, that, whether we wake or sleep, we should live together with him.
10የምንነቃም ብንሆን፥ የምናንቀላፋም ብንሆን፥ ከእርሱ ጋር አብረን በሕይወት እንኖር ዘንድ ስለ እኛ ሞተ።
11Wherefore comfort yourselves together, and edify one another, even as also ye do.
11ስለዚህ እናንተ ደግሞ እንደምታደርጉ፥ እርስ በርሳችሁ ተመካከሩ አንዱም አንዱም ሌላውን ያንጸው።
12And we beseech you, brethren, to know them which labour among you, and are over you in the Lord, and admonish you;
12ወንድሞች ሆይ፥ በመካከላችሁ የሚደክሙትን በጌታም የሚገዙአችሁን የሚገሥጹአችሁንም ታውቁ ዘንድ፥ ስለ ሥራቸውም በፍቅር ከመጠን ይልቅ ታከብሩአቸው ዘንድ እንለምናችኋለን። እርስ በርሳችሁ በሰላም ሁኑ።
13And to esteem them very highly in love for their work's sake. And be at peace among yourselves.
14ወንድሞች ሆይ፥ እንመክራችኋለን፤ ያለ ሥርዓት የሚሄዱትን ገሥጹአቸው፤ ድፍረት የሌላቸውን አጽኑአቸው፤ ለደካሞች ትጉላቸው፤ ሰውን ሁሉ ታገሡ።
14Now we exhort you, brethren, warn them that are unruly, comfort the feebleminded, support the weak, be patient toward all men.
15ማንም ለሌላው በክፉ ፈንታ ክፉ እንዳይመልስ ተጠንቀቁ፥ ነገር ግን ሁልጊዜ እርስ በርሳችሁ ለሁሉም መልካሙን ለማድረግ ትጉ።
15See that none render evil for evil unto any man; but ever follow that which is good, both among yourselves, and to all men.
16ሁልጊዜ ደስ ይበላችሁ፤
16Rejoice evermore.
17ሳታቋርጡ ጸልዩ፤ በሁሉ አመስግኑ፤ ይህ የእግዚአብሔር ፈቃድ በክርስቶስ ኢየሱስ ወደ እናንተ ነውና።
17Pray without ceasing.
19መንፈስን አታጥፉ፤
18In every thing give thanks: for this is the will of God in Christ Jesus concerning you.
20ትንቢትን አትናቁ፤ ሁሉን ፈትኑ መልካሙንም ያዙ፤
19Quench not the Spirit.
22ከማናቸውም ዓይነት ክፉ ነገር ራቁ።
20Despise not prophesyings.
23የሰላምም አምላክ ራሱ ሁለንተናችሁን ይቀድስ፤ መንፈሳችሁም ነፍሳችሁም ሥጋችሁም ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በመጣ ጊዜ ያለ ነቀፋ ፈጽመው ይጠበቁ።
21Prove all things; hold fast that which is good.
24የሚጠራችሁ የታመነ ነው፥ እርሱም ደግሞ ያደርገዋል።
22Abstain from all appearance of evil.
25ወንድሞች ሆይ፥ ስለ እኛ ጸልዩ።
23And the very God of peace sanctify you wholly; and I pray God your whole spirit and soul and body be preserved blameless unto the coming of our Lord Jesus Christ.
26ከወንድሞች ሁሉ ጋር በተቀደሰ አሳሳም ሰላምታ ተሰጣጡ።
24Faithful is he that calleth you, who also will do it.
27ይህ መልእክት ለቅዱሳን ወንድሞች ሁሉ እንዲነበብ በጌታ አምላችኋለሁ።
25Brethren, pray for us.
28የጌታችን የኢየሱስ ክርስቶስ ጸጋ ከእናንተ ጋር ይሁን፤ አሜን።
26Greet all the brethren with an holy kiss.
27I charge you by the Lord that this epistle be read unto all the holy brethren.
28The grace of our Lord Jesus Christ be with you. Amen.