1Now upon the first day of the week, very early in the morning, they came unto the sepulchre, bringing the spices which they had prepared, and certain others with them.
1ነገር ግን ከሳምንቱ በመጀመሪያው ቀን ያዘጋጁትን ሽቱ ይዘው ከእነርሱም ጋር አንዳንዶቹ ወደ መቃብሩ እጅግ ማልደው መጡ።
2And they found the stone rolled away from the sepulchre.
2ድንጋዩንም ከመቃብሩ ተንከባሎ አገኙት፥
3And they entered in, and found not the body of the Lord Jesus.
3ገብተውም የጌታን የኢየሱስን ሥጋ አላገኙም።
4And it came to pass, as they were much perplexed thereabout, behold, two men stood by them in shining garments:
4እነርሱም በዚህ ሲያመነቱ፥ እነሆ፥ ሁለት ሰዎች የሚያንጸባርቅ ልብስ ለብሰው ወደ እነርሱ ቀረቡ፤
5And as they were afraid, and bowed down their faces to the earth, they said unto them, Why seek ye the living among the dead?
5ፈርተውም ፊታቸውን ወደ ምድር አቀርቅረው ሳሉ፥ እንዲህ አሉአቸው። ሕያውን ከሙታን መካከል ስለ ምን ትፈልጋላችሁ? ተነሥቶአል እንጂ በዚህ የለም።
6He is not here, but is risen: remember how he spake unto you when he was yet in Galilee,
6የሰው ልጅ በኃጢአተኞች እጅ አልፎ ሊሰጥና ሊሰቀል በሦስተኛውም ቀን ሊነሣ ግድ ነው እያለ ገና በገሊላ ሳለ ለእናንተ እንደ ተናገረ አስቡ።
7Saying, The Son of man must be delivered into the hands of sinful men, and be crucified, and the third day rise again.
8ቃሎቹንም አሰቡ፥ ከመቃብሩም ተመልሰው ይህን ሁሉ ለአሥራ አንዱና ለሌሎች ሁሉ ነገሩአቸው።
8And they remembered his words,
10ይህንም ለሐዋርያት የነገሩአቸው መግደላዊት ማርያምና ዮሐና የያዕቆብም እናት ማርያም ከእነርሱም ጋር የነበሩት ሌሎች ሴቶች ነበሩ።
9And returned from the sepulchre, and told all these things unto the eleven, and to all the rest.
11ይህም ቃል ቅዠት መስሎ ታያቸውና አላመኑአቸውም።
10It was Mary Magdalene and Joanna, and Mary the mother of James, and other women that were with them, which told these things unto the apostles.
12ጴጥሮስ ግን ተነሥቶ ወደ መቃብር ሮጠ፤ በዚያም ዝቅ ብሎ ሲመለከት የተልባ እግር ልብስን ብቻ አየ፤ በሆነውም ነገር እየተደነቀ ወደ ቤቱ ሄደ።
11And their words seemed to them as idle tales, and they believed them not.
13እነሆም፥ ከእነርሱ ሁለቱ በዚያ ቀን ከኢየሩሳሌም ስድሳ ምዕራፍ ያህል ወደሚርቅ ኤማሁስ ወደሚባል መንደር ይሄዱ ነበር፤
12Then arose Peter, and ran unto the sepulchre; and stooping down, he beheld the linen clothes laid by themselves, and departed, wondering in himself at that which was come to pass.
14ስለዚህም ስለ ሆነው ነገር ሁሉ እርስ በርሳቸው ይነጋገሩ ነበር።
13And, behold, two of them went that same day to a village called Emmaus, which was from Jerusalem about threescore furlongs.
15ሲነጋገሩና ሲመራመሩም፥ ኢየሱስ ራሱ ቀርቦ ከእነርሱ ጋር ይሄድ ነበር፤
14And they talked together of all these things which had happened.
16ነገር ግን እንዳያውቁት ዓይናቸው ተይዞ ነበር።
15And it came to pass, that, while they communed together and reasoned, Jesus himself drew near, and went with them.
17እርሱም። እየጠወለጋችሁ ስትሄዱ፥ እርስ በርሳችሁ የምትነጋገሩአቸው እነዚህ ነገሮች ምንድር ናቸው? አላቸው።
16But their eyes were holden that they should not know him.
18ቀለዮጳ የሚባልም አንዱ መልሶ። አንተ በኢየሩሳሌም እንግዳ ሆነህ ለብቻህ ትኖራለህን? በእነዚህ ቀኖች በዚያ የሆነውን ነገር አታውቅምን? አለው።
17And he said unto them, What manner of communications are these that ye have one to another, as ye walk, and are sad?
19እርሱም። ይህ ምንድር ነው? አላቸው። እነርሱም እንዲህ አሉት። በእግዚአብሔርና በሕዝቡ ሁሉ ፊት በሥራና በቃል ብርቱ ነቢይ ስለ ነበረው ስለ ናዝሬቱ ስለ ኢየሱስ፤
18And the one of them, whose name was Cleopas, answering said unto him, Art thou only a stranger in Jerusalem, and hast not known the things which are come to pass there in these days?
20እርሱንም የካህናት አለቆችና መኳንንቶቻችን ለሞት ፍርድ እንዴት አሳልፈው እንደ ሰጡትና እንደ ሰቀሉት ነው።
19And he said unto them, What things? And they said unto him, Concerning Jesus of Nazareth, which was a prophet mighty in deed and word before God and all the people:
21እኛ ግን እስራኤልን እንዲቤዥ ያለው እርሱ እንደ ሆነ ተስፋ አድርገን ነበር፤ ደግሞም ከዚህ ሁሉ ጋር ይህ ከሆነ ዛሬ ሦስተኛው ቀን ነው።
20And how the chief priests and our rulers delivered him to be condemned to death, and have crucified him.
22ደግሞም ከእኛ ውስጥ ማልደው ከመቃብሩ ዘንድ የነበሩት አንዳንድ ሴቶች አስገረሙን፤
21But we trusted that it had been he which should have redeemed Israel: and beside all this, to day is the third day since these things were done.
23ሥጋውንም ባጡ ጊዜ። ሕያው ነው የሚሉ የመላእክትን ራእይ ደግሞ አየን ሲሉ መጥተው ነበር።
22Yea, and certain women also of our company made us astonished, which were early at the sepulchre;
24ከእኛም ጋር ከነበሩት ወደ መቃብር ሄደው ሴቶች እንደ ተናገሩት ሆኖ አገኙት፥ እርሱን ግን አላዩትም።
23And when they found not his body, they came, saying, that they had also seen a vision of angels, which said that he was alive.
25እርሱም። እናንተ የማታስተውሉ፥ ነቢያትም የተናገሩትን ሁሉ ልባችሁ ከማመን የዘገየ፤
24And certain of them which were with us went to the sepulchre, and found it even so as the women had said: but him they saw not.
26ክርስቶስ ይህን መከራ ይቀበል ዘንድና ወደ ክብሩ ይገባ ዘንድ ይገባው የለምን? አላቸው።
25Then he said unto them, O fools, and slow of heart to believe all that the prophets have spoken:
27ከሙሴና ከነቢያት ሁሉ ጀምሮ ስለ እርሱ በመጻሕፍት ሁሉ የተጻፈውን ተረጐመላቸው።
26Ought not Christ to have suffered these things, and to enter into his glory?
28ወደሚሄዱበትም መንደር ቀረቡ፥ እርሱም ሩቅ የሚሄድ መሰላቸው።
27And beginning at Moses and all the prophets, he expounded unto them in all the scriptures the things concerning himself.
29እነርሱ። ከእኛ ጋር እደር፥ ማታ ቀርቦአልና ቀኑም ሊመሽ ጀምሮአል ብለው ግድ አሉት፤ ከእነርሱም ጋር ሊያድር ገባ።
28And they drew nigh unto the village, whither they went: and he made as though he would have gone further.
30ከእነርሱም ጋር በማዕድ ተቀምጦ ሳለ እንጀራውን አንሥቶ ባረከው፥ ቈርሶም ሰጣቸው፤
29But they constrained him, saying, Abide with us: for it is toward evening, and the day is far spent. And he went in to tarry with them.
31ዓይናቸውም ተከፈተ፥ አወቁትም፤ እርሱም ከእነርሱ ተሰወረ።
30And it came to pass, as he sat at meat with them, he took bread, and blessed it, and brake, and gave to them.
32እርስ በርሳቸውም። በመንገድ ሲናገረን መጻሕፍትንም ሲከፍትልን ልባችን ይቃጠልብን አልነበረምን? ተባባሉ።
31And their eyes were opened, and they knew him; and he vanished out of their sight.
33በዚያችም ሰዓት ተነሥተው ወደ ኢየሩሳሌም ተመለሱ፥ አሥራ አንዱና ከእነርሱ ጋር የነበሩትም። ጌታ በእውነት ተነሥቶአል ለስምዖንም ታይቶአል እያሉ በአንድነት ተሰብስበው አገኙአቸው።
32And they said one to another, Did not our heart burn within us, while he talked with us by the way, and while he opened to us the scriptures?
35እነርሱም በመንገድ የሆነውን እንጀራውንም በቈረሰ ጊዜ እንዴት እንደ ታወቀላቸው ተረኩላቸው።
33And they rose up the same hour, and returned to Jerusalem, and found the eleven gathered together, and them that were with them,
36ይህንም ሲነጋገሩ ኢየሱስ ራሱ በመካከላቸው ቆሞ። ሰላም ለእናንተ ይሁን አላቸው።
34Saying, The Lord is risen indeed, and hath appeared to Simon.
37ነገር ግን ደነገጡና ፈሩ መንፈስም ያዩ መሰላቸው።
35And they told what things were done in the way, and how he was known of them in breaking of bread.
38እርሱም። ስለ ምን ትደነግጣላችሁ? ስለ ምንስ አሳብ በልባችሁ ይነሣል?
36And as they thus spake, Jesus himself stood in the midst of them, and saith unto them, Peace be unto you.
39እኔ ራሴ እንደ ሆንሁ እጆቼንና እግሮቼን እዩ፤ በእኔ እንደምታዩት፥ መንፈስ ሥጋና አጥንት የለውምና እኔን ዳስሳችሁ እዩ አላቸው።
37But they were terrified and affrighted, and supposed that they had seen a spirit.
40ይህንም ብሎ እጆቹንና እግሮቹን አሳያቸው።
38And he said unto them, Why are ye troubled? and why do thoughts arise in your hearts?
41እነርሱም ከደስታ የተነሣ ገና ስላላመኑ ሲደነቁ ሳሉ። በዚህ አንዳች የሚበላ አላችሁን? አላቸው።
39Behold my hands and my feet, that it is I myself: handle me, and see; for a spirit hath not flesh and bones, as ye see me have.
42እነርሱም ከተጠበሰ ዓሣ አንድ ቁራጭ፥ ከማር ወለላም ሰጡት፤
40And when he had thus spoken, he shewed them his hands and his feet.
43ተቀብሎም በፊታቸው በላ።
41And while they yet believed not for joy, and wondered, he said unto them, Have ye here any meat?
44እርሱም። ከእናንተ ጋር ሳለሁ በሙሴ ሕግና በነቢያት በመዝሙራትም ስለ እኔ የተጻፈው ሁሉ ይፈጸም ዘንድ ይገባል ብዬ የነገርኋችሁ ቃሌ ይህ ነው አላቸው።
42And they gave him a piece of a broiled fish, and of an honeycomb.
45በዚያን ጊዜም መጻሕፍትን ያስተውሉ ዘንድ አእምሮአቸውን ከፈተላቸው፤
43And he took it, and did eat before them.
46እንዲህም አላቸው። ክርስቶስ መከራ ይቀበላል በሦስተኛውም ቀን ከሙታን ይነሣል፥
44And he said unto them, These are the words which I spake unto you, while I was yet with you, that all things must be fulfilled, which were written in the law of Moses, and in the prophets, and in the psalms, concerning me.
47በስሙም ንስሐና የኃጢአት ስርየት ከኢየሩሳሌም ጀምሮ በአሕዛብ ሁሉ ይሰበካል ተብሎ እንዲሁ ተጽፎአል።
45Then opened he their understanding, that they might understand the scriptures,
48እናንተም ለዚህ ምስክሮች ናችሁ።
46And said unto them, Thus it is written, and thus it behoved Christ to suffer, and to rise from the dead the third day:
49እነሆም፥ አባቴ የሰጠውን ተስፋ እኔ እልክላችኋለሁ፤ እናንተ ግን ከላይ ኃይል እስክትለብሱ ድረስ በኢየሩሳሌም ከተማ ቆዩ።
47And that repentance and remission of sins should be preached in his name among all nations, beginning at Jerusalem.
50እስከ ቢታንያም አወጣቸው እጆቹንም አንሥቶ ባረካቸው።
48And ye are witnesses of these things.
51ሲባርካቸውም ከእነርሱ ተለየ ወደ ሰማይም ዐረገ።
49And, behold, I send the promise of my Father upon you: but tarry ye in the city of Jerusalem, until ye be endued with power from on high.
52እነርሱም፤ ሰገዱለትና በብዙ ደስታ ወደ ኢየሩሳሌም ተመለሱ፥
50And he led them out as far as to Bethany, and he lifted up his hands, and blessed them.
53ዘወትርም እግዚአብሔርን እያመሰገኑና እየባረኩ በመቅደስ ኖሩ።
51And it came to pass, while he blessed them, he was parted from them, and carried up into heaven.
52And they worshipped him, and returned to Jerusalem with great joy:
53And were continually in the temple, praising and blessing God. Amen.