1The beginning of the gospel of Jesus Christ, the Son of God;
1የእግዚአብሔር ልጅ የኢየሱስ ክርስቶስ ወንጌል መጀመሪያ።
2As it is written in the prophets, Behold, I send my messenger before thy face, which shall prepare thy way before thee.
2እነሆ፥ መንገድህን የሚጠርግ መልክተኛዬን በፊትህ እልካለሁ የጌታን መንገድ አዘጋጁ ጥርጊያውንም አቅኑ እያለ በምድረ በዳ የሚጮኽ ሰው ድምፅ ተብሎ በነቢዩ በኢሳይያስ እንደ ተጻፈ፥
3The voice of one crying in the wilderness, Prepare ye the way of the Lord, make his paths straight.
4ዮሐንስ በምድረ በዳ እያጠመቀ የንስሐንም ጥምቀት ለኃጢአት ስርየት እየሰበከ መጣ።
4John did baptize in the wilderness, and preach the baptism of repentance for the remission of sins.
5የይሁዳም አገር ሁሉ የኢየሩሳሌምም ሰዎች ሁሉ ወደ እርሱ ይወጡ ነበር፥ ኃጢአታቸውንም እየተናዘዙ በዮርዳኖስ ወንዝ ከእርሱ ይጠመቁ ነበር።
5And there went out unto him all the land of Judaea, and they of Jerusalem, and were all baptized of him in the river of Jordan, confessing their sins.
6ዮሐንስም የግመል ጠጉር ለብሶ በወገቡ ጠፍር ይታጠቅ አንበጣና የበረሀ ማርም ይበላ ነበር።
6And John was clothed with camel's hair, and with a girdle of a skin about his loins; and he did eat locusts and wild honey;
7ተጎንብሼ የጫማውን ጠፍር መፍታት የማይገባኝ ከእኔ የሚበረታ በኋላዬ ይመጣል።
7And preached, saying, There cometh one mightier than I after me, the latchet of whose shoes I am not worthy to stoop down and unloose.
8እኔ በውኃ አጠመቅኋችሁ እርሱ ግን በመንፈስ ቅዱስ ያጠምቃችኋል እያለ ይሰብክ ነበር።
8I indeed have baptized you with water: but he shall baptize you with the Holy Ghost.
9በዚያ ወራትም ኢየሱስ ከገሊላ ናዝሬት መጥቶ ከዮሐንስ በዮርዳኖስ ወንዝ ተጠመቀ።
9And it came to pass in those days, that Jesus came from Nazareth of Galilee, and was baptized of John in Jordan.
10ወዲያውም ከውኃው በወጣ ጊዜ ሰማያት ሲቀደዱ መንፈስም እንደ ርግብ ሲወርድበት አየና። የምወድህ ልጄ አንተ ነህ፥
10And straightway coming up out of the water, he saw the heavens opened, and the Spirit like a dove descending upon him:
11በአንተ ደስ ይለኛል የሚል ድምፅ ከሰማያት መጣ።
11And there came a voice from heaven, saying, Thou art my beloved Son, in whom I am well pleased.
12ወዲያውም መንፈስ ወደ ምድረ በዳ አወጣው።
12And immediately the spirit driveth him into the wilderness.
13በምድረ በዳም ከሰይጣን እየተፈተነ አርባ ቀን ሰነበተ ከአራዊትም ጋር ነበረ፥ መላእክቱም አገለገሉት።
13And he was there in the wilderness forty days, tempted of Satan; and was with the wild beasts; and the angels ministered unto him.
14ዮሐንስም አልፎ ከተሰጠ በኋላ ኢየሱስ የእግዚአብሔርን መንግሥት ወንጌል እየሰበከና። ዘመኑ ተፈጸመ የእግዚአብሔርም መንግሥት ቀርባለች ንስሐ ግቡ በወንጌልም እመኑ እያለ ወደ ገሊላ መጣ።
14Now after that John was put in prison, Jesus came into Galilee, preaching the gospel of the kingdom of God,
16በገሊላ ባሕርም አጠገብ ሲያልፍ ስምዖንን ወንድሙንም እንድርያስን መረባቸውን ወደ ባሕር ሲጥሉ አየ፥ ዓሣ አጥማጆች ነበሩና።
15And saying, The time is fulfilled, and the kingdom of God is at hand: repent ye, and believe the gospel.
17ኢየሱስም። በኋላዬ ኑና ሰዎችን አጥማጆች እንድትሆኑ አደርጋችኋለሁ አላቸው።
16Now as he walked by the sea of Galilee, he saw Simon and Andrew his brother casting a net into the sea: for they were fishers.
18ወዲያውም መረባቸውን ትተው ተከተሉት።
17And Jesus said unto them, Come ye after me, and I will make you to become fishers of men.
19ከዚያም ጥቂት እልፍ ብሎ የዘብዴዎስን ልጅ ያዕቆብን ወንድሙንም ዮሐንስን ደግሞ በታንኳ ላይ መረባቸውን ሲያበጁ አየ።
18And straightway they forsook their nets, and followed him.
20ወዲያውም ጠራቸው አባታቸውንም ዘብዴዎስን ከሞያተኞቹ ጋር በታንኳ ላይ ትተው ተከትለውት ሄዱ።
19And when he had gone a little farther thence, he saw James the son of Zebedee, and John his brother, who also were in the ship mending their nets.
21ወደ ቅፍርናሆምም ገቡ፤ ወዲያውም በሰንበት ወደ ምኵራብ ገብቶ አስተማረ።
20And straightway he called them: and they left their father Zebedee in the ship with the hired servants, and went after him.
22እንደ ባለ ሥልጣን ያስተምራቸው ነበር እንጂ እንደ ጻፎች አይደለምና በትምህርቱ ተገረሙ።
21And they went into Capernaum; and straightway on the sabbath day he entered into the synagogue, and taught.
23በዚያን ጊዜም በምኩራባቸው ርኵስ መንፈስ ያለው ሰው ነበረ፤
22And they were astonished at his doctrine: for he taught them as one that had authority, and not as the scribes.
24እርሱም። የናዝሬቱ ኢየሱስ ሆይ፥ ከአንተ ጋር ምን አለን? ልታጠፋን መጣህን? ማን እንደ ሆንህ አውቄአለሁ፥ የእግዚአብሔር ቅዱሱ ብሎ ጮኸ።
23And there was in their synagogue a man with an unclean spirit; and he cried out,
25ኢየሱስም። ዝም በል ከእርሱም ውጣ ብሎ ገሠጸው።
24Saying, Let us alone; what have we to do with thee, thou Jesus of Nazareth? art thou come to destroy us? I know thee who thou art, the Holy One of God.
26ርኵሱም መንፈስ አንፈራገጠውና በታላቅ ድምፅ ጮኾ ከእርሱ ወጣ።
25And Jesus rebuked him, saying, Hold thy peace, and come out of him.
27ሁሉም። ይህ ምንድር ነው? በሥልጣን ርኵሳን መናፍስትን ያዝዛል፤ እነርሱም ይታዘዙለታልና ይህ አዲስ ትምህርት ምንድር ነው? ብለው እስኪጠያየቁ ድረስ አደነቁ።
26And when the unclean spirit had torn him, and cried with a loud voice, he came out of him.
28ዝናውም ወዲያው በየስፍራው ወደ ገሊላ ዙሪያ ሁሉ ወጣ።
27And they were all amazed, insomuch that they questioned among themselves, saying, What thing is this? what new doctrine is this? for with authority commandeth he even the unclean spirits, and they do obey him.
29ወዲያውም ከምኵራብ ወጥቶ ከያዕቆብና ከዮሐንስ ጋር ወደ ስምዖንና ወደ እንድርያስ ቤት ገባ።
28And immediately his fame spread abroad throughout all the region round about Galilee.
30የስምዖንም አማት በንዳድ ታማ ተኝታ ነበር፥ ስለ እርስዋም ወዲያው ነገሩት።
29And forthwith, when they were come out of the synagogue, they entered into the house of Simon and Andrew, with James and John.
31ቀርቦም እጅዋን ይዞ አስነሣት ንዳዱም ወዲያው ለቀቃትና አገለገለቻቸው።
30But Simon's wife's mother lay sick of a fever, and anon they tell him of her.
32ፀሐይም ገብቶ በመሸ ጊዜ፥ የታመሙትንና አጋንንት ያደረባቸውን ሁሉ ወደ እርሱ አመጡ፤
31And he came and took her by the hand, and lifted her up; and immediately the fever left her, and she ministered unto them.
33ከተማይቱም ሁላ በደጅ ተሰብስባ ነበር።
32And at even, when the sun did set, they brought unto him all that were diseased, and them that were possessed with devils.
34በልዩ ልዩ ደዌም የታመሙትን ብዙዎችን ፈወሰ፥ ብዙዎችንም አጋንንት አወጣ፥ አጋንንትም ክርስቶስ መሆኑን አውቀው ነበርና ሊናገሩ አልፈቀደላቸውም።
33And all the city was gathered together at the door.
35ማለዳም ተነሥቶ ገና ሌሊት ሳለ ወጣ ወደ ምድረ በዳም ሄዶ በዚያ ጸለየ።
34And he healed many that were sick of divers diseases, and cast out many devils; and suffered not the devils to speak, because they knew him.
36ስምዖንና ከእርሱ ጋር የነበሩትም ገሥግሠው ተከተሉት፥
35And in the morning, rising up a great while before day, he went out, and departed into a solitary place, and there prayed.
37ባገኙትም ጊዜ። ሁሉ ይፈልጉሃል አሉት።
36And Simon and they that were with him followed after him.
38እርሱም። በዚያ ደግሞ ልሰብክ ወደ ሌላ ስፍራ በቅርብ ወዳሉ መንደሮች እንሂድ ስለዚህ ወጥቻለሁና አላቸው።
37And when they had found him, they said unto him, All men seek for thee.
39በምኵራባቸውም እየሰበከ አጋንንትንም እያወጣ ወደ ገሊላ ሁሉ መጣ።
38And he said unto them, Let us go into the next towns, that I may preach there also: for therefore came I forth.
40ለምጻምም ወደ እርሱ መጥቶ ተንበረከከና። ብትወድስ ልታነጻኝ ትችላለህ ብሎ ለመነው።
39And he preached in their synagogues throughout all Galilee, and cast out devils.
41ኢየሱስም አዘነለት እጁንም ዘርግቶ ዳሰሰውና። እወድዳለሁ፤ ንጻ አለው።
40And there came a leper to him, beseeching him, and kneeling down to him, and saying unto him, If thou wilt, thou canst make me clean.
42በተናገረም ጊዜ ለምጹ ወዲያው ለቀቀውና ነጻ።
41And Jesus, moved with compassion, put forth his hand, and touched him, and saith unto him, I will; be thou clean.
43በብርቱም ተናግሮ ወዲያው አወጣው፤
42And as soon as he had spoken, immediately the leprosy departed from him, and he was cleansed.
44ለማንም አንዳች እንዳትናገር ተጠንቀቅ፥ ነገር ግን ሄደህ ራስህን ለካህን አሳይ ለእነርሱም ምስክር እንዲሆን ስለ መንጻትህ ሙሴ ያዘዘውን አቅርብ አለው።
43And he straitly charged him, and forthwith sent him away;
45እርሱ ግን ሲወጣ ብዙ ሊሰብክና ነገሩን ሊያወራ ጀመረ፥ ስለዚህም ኢየሱስ ተገልጦ ወደ ከተማ መግባት ወደ ፊት ተሳነው፥ ነገር ግን በውጭ በምድረ በዳ ይኖር ነበር፤ ከየስፍራውም ወደ እርሱ ይመጡ ነበር።
44And saith unto him, See thou say nothing to any man: but go thy way, shew thyself to the priest, and offer for thy cleansing those things which Moses commanded, for a testimony unto them.
45But he went out, and began to publish it much, and to blaze abroad the matter, insomuch that Jesus could no more openly enter into the city, but was without in desert places: and they came to him from every quarter.