Young`s Literal Translation

Amharic: New Testament

1 John

2

1My little children, these things I write to you, that ye may not sin: and if any one may sin, an advocate we have with the Father, Jesus Christ, a righteous one,
1ልጆቼ ሆይ፥ ኃጢአትን እንዳታደርጉ ይህን እጽፍላችኋለሁ። ማንም ኃጢአትን ቢያደርግ ከአብ ዘንድ ጠበቃ አለን እርሱም ጻድቅ የሆነ ኢየሱስ ክርስቶስ ነው።
2and he — he is a propitiation for our sins, and not for ours only, but also for the whole world,
2እርሱም የኃጢአታችን ማስተስሪያ ነው፥ ለኃጢአታችንም ብቻ አይደለም፥ ነገር ግን ለዓለሙ ሁሉ ኃጢአት እንጂ።
3and in this we know that we have known him, if his commands we may keep;
3ትእዛዛቱንም ብንጠብቅ በዚህ እንዳወቅነው እናውቃለን።
4he who is saying, `I have known him,` and his command is not keeping, a liar he is, and in him the truth is not;
4አውቄዋለሁ የሚል ትእዛዛቱንም የማይጠብቅ ውሸተኛ ነው እውነትም በእርሱ ውስጥ የለም።
5and whoever may keep his word, truly in him the love of God hath been perfected; in this we know that in him we are.
5ቃሉን ግን የሚጠብቅ ሁሉ በእርሱ የእግዚአብሔር ፍቅር በእውነት ተፈጽሞአል። በእርሱ እንዳለን በዚህ እናውቃለን፤
6He who is saying in him he doth remain, ought according as he walked also himself so to walk.
6በእርሱ እኖራለሁ የሚል እርሱ እንደ ተመላለሰ ራሱ ደግሞ ሊመላለስ ይገባዋል።
7Brethren, a new command I write not to you, but an old command, that ye had from the beginning — the old command is the word that ye heard from the beginning;
7ወንድሞች ሆይ፥ ከመጀመሪያ የነበረቻችሁ አሮጌ ትእዛዝ እንጂ የምጽፍላችሁ አዲስ ትእዛዝ አይደለችም፤ አሮጌይቱ ትእዛዝ የሰማችኋት ቃል ናት።
8again, a new command I write to you, which thing is true in him and in you, because the darkness doth pass away, and the true light doth now shine;
8ዳግመኛ አዲስ ትእዛዝን እጽፍላችኋለሁ፥ ይህም ነገር በእርሱ በእናንተም እውነተኛ ነው፤ ጨለማው ያልፋልና እውነተኛውም ብርሃን አሁን ይበራል።
9he who is saying, in the light he is, and his brother is hating, in the darkness he is till now;
9በብርሃን አለሁ የሚል ወንድሙንም የሚጠላ እስከ አሁን በጨለማ አለ።
10he who is loving his brother, in the light he doth remain, and a stumbling-block in him there is not;
10ወንድሙንም የሚወድ በብርሃን ይኖራል ማሰናከያም የለበትም፤
11and he who is hating his brother, in the darkness he is, and in the darkness he doth walk, and he hath not known whither he doth go, because the darkness did blind his eyes.
11ወንድሙን የሚጠላ ግን በጨለማ አለ፥ በጨለማም ይመላለሳል፥ የሚሄድበትንም አያውቅም፥ ጨለማው ዓይኖቹን አሳውሮታልና።
12I write to you, little children, because the sins have been forgiven you through his name;
12ልጆች ሆይ፥ ኃጢአታችሁ ስለ ስሙ ተሰርዮላችኋልና እጽፍላችኋለሁ።
13I write to you, fathers, because ye have known him who [is] from the beginning; I write to you, young men, because ye have overcome the evil. I write to you, little youths, because ye have known the Father:
13አባቶች ሆይ፥ ከመጀመሪያ የነበረውን አውቃችኋልና እጽፍላችኋለሁ። ጎበዞች ሆይ፥ ክፉውን አሸንፋችኋልና እጽፍላችኋለሁ። ልጆች ሆይ፥ አብን አውቃችኋልና እጽፍላችኋለሁ።
14I did write to you, fathers, because ye have known him who [is] from the beginning; I did write to you, young men, because ye are strong, and the word of God in you doth remain, and ye have overcome the evil.
14አባቶች ሆይ፥ ከመጀመሪያ የነበረውን አውቃችኋልና እጽፍላችኋለሁ። ጐበዞች ሆይ፥ ብርቱዎች ስለ ሆናችሁ የእግዚአብሔርም ቃል በእናንተ ስለሚኖር ክፉውንም ስለ አሸነፋችሁ እጽፍላችኋለሁ።
15Love not ye the world, nor the things in the world; if any one doth love the world, the love of the Father is not in him,
15ዓለምን ወይም በዓለም ያሉትን አትውደዱ፤ በዓለም ያለው ሁሉ እርሱም የሥጋ ምኞትና የዓይን አምሮት ስለ ገንዘብም መመካት ከዓለም ስለ ሆነ እንጂ ከአባት ስላልሆነ፥ ማንም ዓለምን ቢወድ የአባት ፍቅር በእርሱ ውስጥ የለም።
16because all that [is] in the world — the desire of the flesh, and the desire of the eyes, and the ostentation of the life — is not of the Father, but of the world,
17ዓለሙም ምኞቱም ያልፋሉ፤ የእግዚአብሔርን ፈቃድ የሚያደርግ ግን ለዘላለም ይኖራል።
17and the world doth pass away, and the desire of it, and he who is doing the will of God, he doth remain — to the age.
18ልጆች ሆይ፥ መጨረሻው ሰዓት ነው፥ የክርስቶስም ተቃዋሚ ይመጣ ዘንድ እንደ ሰማችሁ አሁን እንኳ ብዙዎች የክርስቶስ ተቃዋሚዎች ተነሥተዋል፤ ስለዚህም መጨረሻው ሰዓት እንደ ሆነ እናውቃለን።
18Little youths, it is the last hour; and even as ye heard that the antichrist doth come, even now antichrists have become many — whence we know that it is the last hour;
19ከእኛ ዘንድ ወጡ፥ ዳሩ ግን ከእኛ ወገን አልነበሩም፤ ከእኛ ወገንስ ቢሆኑ ከእኛ ጋር ጸንተው በኖሩ ነበር፤ ነገር ግን ሁሉ ከእኛ ወገን እንዳልሆኑ ይገለጡ ዘንድ ወጡ።
19out of us they went forth, but they were not of us, for if they had been of us, they would have remained with us; but — that they might be manifested that they are not all of us.
20እናንተም ከቅዱሱ ቅባት ተቀብላችኋል፥ ሁሉንም ታውቃላችሁ።
20And ye have an anointing from the Holy One, and have known all things;
21እውነትን የምታውቁ ስለ ሆናችሁ፥ ውሸትም ሁሉ ከእውነት እንዳልሆነ ስለምታውቁ እንጂ እውነትን ስለማታውቁ አልጽፍላችሁም።
21I did not write to you because ye have not known the truth, but because ye have known it, and because no lie is of the truth.
22ክርስቶስ አይደለም ብሎ ኢየሱስን ከሚክድ በቀር ውሸተኛው ማን ነው? አብንና ወልድን የሚክድ ይህ የክርስቶስ ተቃዋሚ ነው።
22Who is the liar, except he who is denying that Jesus is the Christ? this one is the antichrist who is denying the Father and the Son;
23ወልድን የሚክድ ሁሉ አብ እንኳ የለውም፤ በወልድ የሚታመን አብ ደግሞ አለው።
23every one who is denying the Son, neither hath he the Father, [he who is confessing the Son hath the Father also.]
24እናንተስ ከመጀመሪያ የሰማችሁት በእናንተ ጸንቶ ይኑር። ከመጀመሪያ የሰማችሁት በእናንተ ቢኖር፥ እናንተ ደግሞ በወልድና በአብ ትኖራላችሁ።
24Ye, then, that which ye heard from the beginning, in you let it remain; if in you may remain that which from the beginning ye did hear, ye also in the Son and in the Father shall remain,
25እርሱም የሰጠን ተስፋ ይህ የዘላለም ሕይወት ነው።
25and this is the promise that He did promise us — the life the age-during.
26ስለሚያስቱአችሁ ሰዎች ይህን ጽፌላችኋለሁ።
26These things I did write to you concerning those leading you astray;
27እናንተስ ከእርሱ የተቀበላችሁት ቅባት በእናንተ ይኖራል፥ ማንም ሊያስተምራችሁ አያስፈልጋችሁም፤ ነገር ግን የእርሱ ቅባት ስለ ሁሉ እንደሚያስተምራችሁ፥ እውነተኛም እንደ ሆነ ውሸትም እንዳልሆነ፥ እናንተንም እንዳስተማራችሁ፥ በእርሱ ኑሩ።
27and you, the anointing that ye did receive from him, in you it doth remain, and ye have no need that any one may teach you, but as the same anointing doth teach you concerning all, and is true, and is not a lie, and even as was taught you, ye shall remain in him.
28አሁንም፥ ልጆች ሆይ፥ በሚገለጥበት ጊዜ እምነት እንዲሆንልን በመምጣቱም በእርሱ ፊት እንዳናፍር በእርሱ ኑሩ።
28And now, little children, remain in him, that when he may be manifested, we may have boldness, and may not be ashamed before him, in his presence;
29ጻድቅ እንደ ሆነ ካወቃችሁ ጽድቅን የሚያደርግ ሁሉ ከእርሱ እንደ ተወለደ እወቁ።
29if ye know that he is righteous, know ye that every one doing the righteousness, of him hath been begotten.