Young`s Literal Translation

Amharic: New Testament

1 Thessalonians

5

1And concerning the times and the seasons, brethren, ye have no need of my writing to you,
1ወንድሞች ሆይ፥ ስለ ዘመናትና ስለ ወራት ምንም እንዲጻፍላችሁ አያስፈልጋችሁም፤
2for yourselves have known thoroughly that the day of the Lord as a thief in the night doth so come,
2የጌታ ቀን፥ ሌባ በሌሊት እንደሚመጣ፥ እንዲሁ ይመጣ ዘንድ ራሳችሁ አጥብቃችሁ አውቃችኋልና።
3for when they may say, Peace and surety, then sudden destruction doth stand by them, as the travail [doth] her who is with child, and they shall not escape;
3ሰላምና ደኅንነት ነው ሲሉ ያን ጊዜ ምጥ እርጕዝን እንደሚይዛት ጥፋት በድንገት ይመጣባቸዋል ከቶም አያመልጡም።
4and ye, brethren, are not in darkness, that the day may catch you as a thief;
4እናንተ ግን፥ ወንድሞች ሆይ፥ ቀኑ እንደ ሌባ ይደርስባችሁ ዘንድ በጨለማ አይደላችሁም፥
5all ye are sons of light, and sons of day; we are not of night, nor of darkness,
5ሁላችሁ የብርሃን ልጆች የቀንም ልጆች ናችሁና። እኛ ከሌሊት ወይም ከጨለማ አይደለንም፤
6so, then, we may not sleep as also the others, but watch and be sober,
6እንግዲያስ እንንቃ በመጠንም እንኑር እንጂ እንደ ሌሎች አናንቀላፋ።
7for those sleeping, by night do sleep, and those making themselves drunk, by night are drunken,
7የሚያንቀላፉ በሌሊት ያንቀላፋሉና፥ የሚሰክሩም በሌሊት ይሰክራሉና፤
8and we, being of the day — let us be sober, putting on a breastplate of faith and love, and an helmet — a hope of salvation,
8እኛ ግን ከቀን ስለ ሆንን፥ የእምነትንና የፍቅርን ጥሩር የመዳንንም ተስፋ እንደ ራስ ቁር እየለበስን በመጠን እንኑር፤
9because God did not appoint us to anger, but to the acquiring of salvation through our Lord Jesus Christ,
9እግዚአብሔር ለቍጣ አልመረጠንምና፥ በጌታችን በኢየሱስ ክርስቶስ መዳንን ለማግኘት ነው እንጂ።
10who did die for us, that whether we wake — whether we sleep — together with him we may live;
10የምንነቃም ብንሆን፥ የምናንቀላፋም ብንሆን፥ ከእርሱ ጋር አብረን በሕይወት እንኖር ዘንድ ስለ እኛ ሞተ።
11wherefore, comfort ye one another, and build ye up, one the one, as also ye do.
11ስለዚህ እናንተ ደግሞ እንደምታደርጉ፥ እርስ በርሳችሁ ተመካከሩ አንዱም አንዱም ሌላውን ያንጸው።
12And we ask you, brethren, to know those labouring among you, and leading you in the Lord, and admonishing you,
12ወንድሞች ሆይ፥ በመካከላችሁ የሚደክሙትን በጌታም የሚገዙአችሁን የሚገሥጹአችሁንም ታውቁ ዘንድ፥ ስለ ሥራቸውም በፍቅር ከመጠን ይልቅ ታከብሩአቸው ዘንድ እንለምናችኋለን። እርስ በርሳችሁ በሰላም ሁኑ።
13and to esteem them very abundantly in love, because of their work; be at peace among yourselves;
14ወንድሞች ሆይ፥ እንመክራችኋለን፤ ያለ ሥርዓት የሚሄዱትን ገሥጹአቸው፤ ድፍረት የሌላቸውን አጽኑአቸው፤ ለደካሞች ትጉላቸው፤ ሰውን ሁሉ ታገሡ።
14and we exhort you, brethren, admonish the disorderly, comfort the feeble-minded, support the infirm, be patient unto all;
15ማንም ለሌላው በክፉ ፈንታ ክፉ እንዳይመልስ ተጠንቀቁ፥ ነገር ግን ሁልጊዜ እርስ በርሳችሁ ለሁሉም መልካሙን ለማድረግ ትጉ።
15see no one evil for evil may render to any one, but always that which is good pursue ye, both to one another and to all;
16ሁልጊዜ ደስ ይበላችሁ፤
16always rejoice ye;
17ሳታቋርጡ ጸልዩ፤ በሁሉ አመስግኑ፤ ይህ የእግዚአብሔር ፈቃድ በክርስቶስ ኢየሱስ ወደ እናንተ ነውና።
17continually pray ye;
19መንፈስን አታጥፉ፤
18in every thing give thanks, for this [is] the will of God in Christ Jesus in regard to you.
20ትንቢትን አትናቁ፤ ሁሉን ፈትኑ መልካሙንም ያዙ፤
19The Spirit quench not;
22ከማናቸውም ዓይነት ክፉ ነገር ራቁ።
20prophesyings despise not;
23የሰላምም አምላክ ራሱ ሁለንተናችሁን ይቀድስ፤ መንፈሳችሁም ነፍሳችሁም ሥጋችሁም ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በመጣ ጊዜ ያለ ነቀፋ ፈጽመው ይጠበቁ።
21all things prove; that which is good hold fast;
24የሚጠራችሁ የታመነ ነው፥ እርሱም ደግሞ ያደርገዋል።
22from all appearance of evil abstain ye;
25ወንድሞች ሆይ፥ ስለ እኛ ጸልዩ።
23and the God of the peace Himself sanctify you wholly, and may your whole spirit, and soul, and body, be preserved unblameably in the presence of our Lord Jesus Christ;
26ከወንድሞች ሁሉ ጋር በተቀደሰ አሳሳም ሰላምታ ተሰጣጡ።
24stedfast is He who is calling you, who also will do [it].
27ይህ መልእክት ለቅዱሳን ወንድሞች ሁሉ እንዲነበብ በጌታ አምላችኋለሁ።
25Brethren, pray for us;
28የጌታችን የኢየሱስ ክርስቶስ ጸጋ ከእናንተ ጋር ይሁን፤ አሜን።
26salute all the brethren in an holy kiss;
27I charge you [by] the Lord, that the letter be read to all the holy brethren;
28the grace of our Lord Jesus Christ [is] with you! Amen.