Young`s Literal Translation

Amharic: New Testament

2 Corinthians

2

1And I decided this to myself, not again to come in sorrow unto you,
1ነገር ግን ዳግመኛ በኀዘን ወደ እናንተ እንዳልመጣ ስለ እኔ ቆረጥሁ።
2for if I make you sorry, then who is he who is making me glad, except he who is made sorry by me?
2እኔስ ባሳዝናችሁ፥ እንግዲያስ በእኔ ምክንያት ከሚያዝን በቀር ደስ የሚያሰኘኝ ማን ነው?
3and I wrote to you this same thing, that having come, I may not have sorrow from them of whom it behoved me to have joy, having confidence in you all, that my joy is of you all,
3ደስ ሊያሰኙኝ ከሚገባቸውም በመምጣቴ ኀዘን እንዳይሆንብኝ ይህንኑ ጻፍሁላችሁ፥ ደስታዬ የሁላችሁ ደስታ ነው ብዬ በሁላችሁ ታምኜአለሁና።
4for out of much tribulation and pressure of heart I wrote to you through many tears, not that ye might be made sorry, but that ye might know the love that I have more abundantly toward you.
4በብዙ መከራና ከልብ ጭንቀት በብዙም እንባ ጽፌላችሁ ነበርና፤ ይህም እናንተን አብዝቼ የምወድበትን ፍቅር እንድታውቁ እንጂ እንዳሳዝናችሁ አይደለም።
5And if any one hath caused sorrow, he hath not caused sorrow to me, but in part, that I may not burden you all;
5ነገር ግን ማንም አሳዝኖ ቢሆን፥ እንዳልከብድባችሁ፥ በክፍል ሁላችሁን እንጂ እኔን ያሳዘነ አይደለም።
6sufficient to such a one is this punishment, that [is] by the more part,
6እንደዚህ ላለ ሰው ይህ ከእናንተ የምትበዙት የቀጣችሁት ቅጣት ይበቃዋልና እንደዚህ ያለው ከልክ በሚበዛ ኀዘን እንዳይዋጥ፥
7so that, on the contrary, [it is] rather for you to forgive and to comfort, lest by over abundant sorrow such a one may be swallowed up;
7ይልቅ ተመልሳችሁ ይቅር ማለትና ማጽናናት ይገባችኋል።
8wherefore, I call upon you to confirm love to him,
8ስለዚህ ከእርሱ ጋር ፍቅርን እንድታጸኑ እለምናችኋለሁ፤
9for, for this also did I write, that I might know the proof of you, whether in regard to all things ye are obedient.
9ስለዚህ ደግሞ ጽፌ ነበርና፤ በሁሉ የምትታዘዙ እንደ ሆናችሁ የእናንተን መፈተን አውቅ ዘንድ አሳቤ ነበር።
10And to whom ye forgive anything — I also; for I also, if I have forgiven anything, to whom I have forgiven [it], because of you — in the person of Christ — [I forgive it,]
10እናንተ ግን ይቅር የምትሉትን እኔ ደግሞ ይቅር እለዋለሁ፤ እኔም ይቅር ካልሁ፥ ይቅር ያልሁትን ስለ እናንተ በክርስቶስ ፊት ይቅር ብዬአለሁ፥
11that we may not be over-reached by the Adversary, for of his devices we are not ignorant.
11በሰይጣን እንዳንታለል፤ የእርሱን አሳብ አንስተውምና።
12And having come to Troas for the good news of the Christ, and a door to me having been opened in the Lord,
12ስለ ክርስቶስም ወንጌል ወደ ጢሮአዳ በመጣሁ ጊዜ፥ ለጌታ ሥራ በር ምንም ቢከፈትልኝ፥ ቲቶን ወንድሜን ስላላገኘሁት መንፈሴ ዕረፍት አልነበረውም፥
13I have not had rest to my spirit, on my not finding Titus my brother, but having taken leave of them, I went forth to Macedonia;
13ነገር ግን ከእነርሱ ተሰናብቼ ወደ መቄዶንያ ወጣሁ።
14and to God [are] thanks, who at all times is leading us in triumph in the Christ, and the fragrance of His knowledge He is manifesting through us in every place,
14ነገር ግን በክርስቶስ ሁልጊዜ ድል በመንሣቱ ለሚያዞረን በእኛም በየስፍራው ሁሉ የእውቀቱን ሽታ ለሚገልጥ ለአምላክ ምስጋና ይሁን፤
15because of Christ a sweet fragrance we are to God, in those being saved, and in those being lost;
15በሚድኑቱና በሚጠፉቱ ዘንድ ለእግዚአብሔር የክርስቶስ መዓዛ ነንና፤
16to the one, indeed, a fragrance of death to death, and to the other, a fragrance of life to life; and for these things who is sufficient?
16ለእነዚህ ለሞት የሚሆን የሞት ሽታ ለእነዚያም ለሕይወት የሚሆን የሕይወት ሽታ ነን። ለዚህም ነገር የሚበቃ ማን ነው?
17for we are not as the many, adulterating the word of God, but as of sincerity — but as of God; in the presence of God, in Christ we do speak.
17የእግዚአብሔርን ቃል ቀላቅለው እንደሚሸቃቅጡት እንደ ብዙዎቹ አይደለንምና፤ በቅንነት ግን ከእግዚአብሔር እንደ ተላክን በእግዚአብሔር ፊት በክርስቶስ ሆነን እንናገራለን።