Young`s Literal Translation

Amharic: New Testament

2 Corinthians

9

1For, indeed, concerning the ministration that [is] for the saints, it is superfluous for me to write to you,
1ለቅዱሳን ስለሚሆነው አገልግሎት ልጽፍላችሁ አያስፈልግምና፤
2for I have known your readiness of mind, which in your behalf I boast of to Macedonians, that Achaia hath been prepared a year ago, and the zeal of you did stir up the more part,
2በጎ ፈቃዳችሁን አውቄአለሁና፤ ስለዚህም። አካይያ ከአምና ጀምሮ ተዘጋጅቶአል ብዬ ለመቄዶንያ ሰዎች በእናንተ እመካለሁ፥ ቅንዓታችሁም የሚበዙቱን አነሣሥቶአል።
3and I sent the brethren, that our boasting on your behalf may not be made vain in this respect; that, according as I said, ye may be ready,
3ነገር ግን ለእነርሱ እንዳልሁ፥ የተዘጋጃችሁ ትሆኑ ዘንድ በዚህም ነገር ስለ እናንተ ያለው ትምክህታችን ከንቱ እንዳይሆን ወንድሞችን እልካለሁ፤
4lest if Macedonians may come with me, and find you unprepared, we — we may be put to shame (that we say not — ye) in this same confidence of boasting.
4ምናልባት የመቄዶንያ ሰዎች ከእኔ ጋር ቢመጡ፥ ያልተዘጋጃችሁም ሆናችሁ ቢያገኙአችሁ፥ እናንተ እንድታፍሩ አላልንም እኛ ግን በዚህ እምነታችን እንድናፍር አይሁን።
5Necessary, therefore, I thought [it] to exhort the brethren, that they may go before to you, and may make up before your formerly announced blessing, that this be ready, as a blessing, and not as covetousness.
5እንግዲህ እንደ በረከት ሆኖ ከስስት የማይሆን ይህ የተዘጋጀ ይሆን ዘንድ አስቀድመው ወደ እናንተ መጥተው፥ አስቀድማችሁ ተስፋ የሰጣችሁትን በረከት አስቀድመው እንዲፈጽሙ ወንድሞችን እለምን ዘንድ እንዲያስፈልገኝ አሰብሁ።
6And this: He who is sowing sparingly, sparingly also shall reap; and he who is sowing in blessings, in blessings also shall reap;
6ይህንም እላለሁ። በጥቂት የሚዘራ በጥቂት ደግሞ ያጭዳል፥ በበረከትም የሚዘራ በበረከት ደግሞ ያጭዳል።
7each one, according as he doth purpose in heart, not out of sorrow or out of necessity, for a cheerful giver doth God love,
7እግዚአብሔር በደስታ የሚሰጠውን ይወዳልና እያንዳንዱ በልቡ እንዳሰበ ይስጥ፥ በኀዘን ወይም በግድ አይደለም።
8and God [is] able all grace to cause to abound to you, that in every thing always all sufficiency having, ye may abound to every good work,
8በተነ፥ ለምስኪኖች ሰጠ፥ ጽድቁ ለዘላለም ይኖራል ተብሎ እንደ ተጻፈ፥ እግዚአብሔር፥ ሁልጊዜ በነገር ሁሉ ብቃትን ሁሉ አግኝታችሁ ለበጎ ሥራ ሁሉ ትበዙ ዘንድ፥ ጸጋን ሁሉ ሊያበዛላችሁ ይችላል።
9(according as it hath been written, `He dispersed abroad, he gave to the poor, his righteousness doth remain to the age,`)
10ለዘሪ ዘርን ለመብላትም እንጀራን በብዙ የሚሰጥ እርሱም የምትዘሩትን ዘር ይሰጣችኋል ያበረክትላችሁማል፥ የጽድቃችሁንም ፍሬ ያሳድጋል፤
10and may He who is supplying seed to the sower, and bread for food, supply and multiply your seed sown, and increase the fruits of your righteousness,
11በእኛ በኩል ለእግዚአብሔር የምስጋና ምክንያት የሚሆነውን ልግስና ሁሉ እንድታሳዩ በሁሉ ነገር ባለ ጠጎች ትሆናላችሁ።
11in every thing being enriched to all liberality, which doth work through us thanksgiving to God,
12የዚህ ረድኤት አገልግሎት ለቅዱሳን የሚጎድላቸውን በሙሉ የሚሰጥ ብቻ አይደለምና፥ ነገር ግን ደግሞ በብዙ ምስጋና ለእግዚአብሔር ይበዛል፤
12because the ministration of this service not only is supplying the wants of the saints, but is also abounding through many thanksgivings to God,
13በዚህ አገልግሎት ስለ ተፈተናችሁ፥ በክርስቶስ ወንጌል በማመናችሁ ስለሚሆን መታዘዝ እነርሱንና ሁሉንም ስለምትረዱበት ልግስና እግዚአብሔርን ያከብራሉ፥
13through the proof of this ministration glorifying God for the subjection of your confession to the good news of the Christ, and [for] the liberality of the fellowship to them and to all,
14ራሳቸውም ስለ እናንተ ሲያማልዱ፥ በእናንተ ላይ ከሚሆነው ከሚበልጠው ከእግዚአብሔር ጸጋ የተነሣ ይናፍቁአችኋል።
14and by their supplication in your behalf, longing after you because of the exceeding grace of God upon you;
15ስለማይነገር ስጦታው እግዚአብሔር ይመስገን።
15thanks also to God for His unspeakable gift!