Young`s Literal Translation

Amharic: New Testament

2 John

1

1The Elder to the choice Kyria, and to her children, whom I love in truth, and not I only, but also all those having known the truth,
1በእኛ ስለሚኖርና ከእኛ ጋር ለዘላለም ስለሚሆን እውነት፥ እኔ ሽማግሌው በእውነት ለምወዳቸውና እኔ ብቻ ሳልሆን እውነትን የሚያውቁ ሁሉ ደግሞ ለሚወዱአቸው ለተመረጠች እመቤትና ለልጆችዋ፤
2because of the truth that is remaining in us, and with us shall be to the age,
3ከእግዚአብሔር አብና ከአብ ልጅ ከኢየሱስ ክርስቶስ ጸጋና ምሕረት ሰላምም በእውነትና በፍቅር ከእኛ ጋር ይሆናሉ።
3there shall be with you grace, kindness, peace, from God the Father, and from the Lord Jesus Christ, the Son of the Father, in truth and love.
4ትእዛዝን ከአብ እንደ ተቀበልን ከልጆችሽ በእውነት የሚሄዱ አንዳንዶችን ስለ አገኘኋቸው እጅግ ደስ ብሎኛል።
4I rejoiced exceedingly that I have found of thy children walking in truth, even as a command we did receive from the Father;
5አሁንም፥ እመቤት ሆይ፥ እርስ በርሳችን እንድንዋደድ እለምንሻለሁ፤ ይህች ከመጀመሪያ በእኛ ዘንድ የነበረች ትእዛዝ ናት እንጂ አዲስ ትእዛዝን እንደምጽፍልሽ አይደለም።
5and now I beseech thee, Kyria, not as writing to thee a new command, but which we had from the beginning, that we may love one another,
6እንደ ትእዛዛቱም እንሄድ ዘንድ ይህ ፍቅር ነው፤ ከመጀመሪያ እንደ ሰማችሁ፥ በእርስዋ ትሄዱ ዘንድ ትእዛዙ ይህች ናት።
6and this is the love, that we may walk according to His commands; this is the command, even as ye did hear from the beginning, that in it ye may walk,
7ብዙ አሳቾች ወደ ዓለም ገብተዋልና እነርሱም ኢየሱስ ክርስቶስ በሥጋ እንደ መጣ የማያምኑ ናቸው፤ ይህ አሳቹና የክርስቶስ ተቃዋሚው ነው።
7because many leading astray did enter into the world, who are not confessing Jesus Christ coming in flesh; this one is he who is leading astray, and the antichrist.
8ሙሉ ደመወዝን እንድትቀበሉ እንጂ የሠራችሁትን እንዳታጠፉ ለራሳችሁ ተጠንቀቁ።
8See to yourselves that ye may not lose the things that we wrought, but a full reward may receive;
9ለሚወጣ ሁሉ በክርስቶስም ትምህርት ለማይኖር ሰው አምላክ የለውም፤ በክርስቶስ ትምህርት ለሚኖር አብና ወልድ አሉት።
9every one who is transgressing, and is not remaining in the teaching of the Christ, hath not God; he who is remaining in the teaching of the Christ, this one hath both the Father and the Son;
10ማንም ወደ እናንተ ቢመጣ ይህንም ትምህርት ባያመጣ በቤታችሁ አትቀበሉት ሰላምም አትበሉት፤
10if any one doth come unto you, and this teaching doth not bear, receive him not into the house, and say not to him, `Hail!`
11ሰላም የሚለው ሰው በክፉ ሥራው ይካፈላልና።
11for he who is saying to him, `Hail,` hath fellowship with his evil works.
12እንድጽፍላችሁ የምፈልገው ብዙ ነገር ሳለኝ በወረቀትና በቀለም ልጽፈው አልወድም፥ ዳሩ ግን ደስታችሁ ፍጹም እንዲሆን ወደ እናንተ ልመጣ አፍ ለአፍም ልናገራችሁ ተስፋ አደርጋለሁ።
12Many things having to write to you, I did not intend through paper and ink, but I hope to come unto you, and speak mouth to mouth, that our joy may be full;
13የተመረጠችው የእኅትሽ ልጆች ሰላምታ ያቀርቡልሻል።
13salute thee do the children of thy choice sister. Amen.