Young`s Literal Translation

Amharic: New Testament

2 Thessalonians

3

1As to the rest, pray ye, brethren, concerning us, that the word of the Lord may run and may be glorified, as also with you,
1በቀረውስ፥ ወንድሞች ሆይ፥ የጌታ ቃል እንዲሮጥ በእናንተም ዘንድ ደግሞ እንደሚሆን እንዲከበር፥ እምነትም ለሁሉ ስለማይሆን ከዓመፀኞችና ከክፉዎች ሰዎች እንድንድን ስለ እኛ ጸልዩ።
2and that we may be delivered from the unreasonable and evil men, for the faith [is] not of all;
3ነገር ግን የሚያጸናችሁ ከክፉውም የሚጠብቃችሁ ጌታ የታመነ ነው።
3and stedfast is the Lord, who shall establish you, and shall guard [you] from the evil;
4የምናዛችሁንም አሁን እንድታደርጉ ወደ ፊትም ደግሞ እንድታደርጉ ስለ እናንተ በጌታ ታምነናል።
4and we have confidence in the Lord touching you, that the things that we command you ye both do and will do;
5ጌታም ወደ እግዚአብሔር ፍቅር ወደ ክርስቶስም ትዕግሥት ልባችንን ያቅናው።
5and the Lord direct your hearts to the love of God, and to the endurance of the Christ.
6ወንድሞች ሆይ፥ ከእኛ እንደ ተቀበለው ወግ ሳይሆን ያለ ሥርዓት ከሚሄድ ወንድም ሁሉ ትለዩ ዘንድ በጌታችን በኢየሱስ ክርስቶስ ስም እናዛችኋለን።
6And we command you, brethren, in the name of our Lord Jesus Christ, to withdraw yourselves from every brother disorderly walking, and not after the deliverance that ye received from us,
7እኛን ልትመስሉ እንዴት እንደሚገባችሁ ራሳችሁ ታውቃላችሁና፤ በእናንተ ዘንድ ያለ ሥርዓት አልሄድንምና፤
7for yourselves have known how it behoveth [you] to imitate us, because we did not act disorderly among you;
8ከእናንተ ዘንድ በአንዱ ስንኳ እንዳንከብድበት፥ ሌሊትና ቀን በድካምና በጥረት እየሠራን እንኖር ነበር እንጂ፥ ከማንም እንጀራን እንዲያው አልበላንም።
8nor for nought did we eat bread of any one, but in labour and in travail, night and day working, not to be chargeable to any of you;
9ይህም እኛን ልትመስሉ ራሳችንን እንደ ምሳሌ እንሰጣችሁ ዘንድ ነበር እንጂ፥ ያለ ሥልጣን ስለ ሆንን አይደለም።
9not because we have not authority, but that ourselves a pattern we might give to you, to imitate us;
10ደግሞ ከእናንተ ጋር ሳለን። ሊሠራ የማይወድ አይብላ ብለን አዘናችሁ ነበርና።
10for even when we were with you, this we did command you, that if any one is not willing to work, neither let him eat,
11ሥራ ከቶ ሳይሠሩ፥ በሰው ነገር እየገቡ፥ ያለ ሥርዓት ከእናንተ ዘንድ ስለሚሄዱ ስለ አንዳንዶች ሰምተናልና።
11for we hear of certain walking among you disorderly, nothing working, but over working,
12እንደነዚህ ያሉትንም በጸጥታ እየሠሩ የገዛ እንጀራቸውን ይበሉ ዘንድ በጌታችን በኢየሱስ ክርስቶስ እናዛቸዋለን እንመክራቸውማለን።
12and such we command and exhort through our Lord Jesus Christ, that with quietness working, their own bread they may eat;
13እናንተ ግን፥ ወንድሞች ሆይ፥ መልካም ሥራን ለመሥራት አትታክቱ።
13and ye, brethren, may ye not be weary doing well,
14በዚህ መልእክት ለተላከ ቃላችን የማይታዘዝ ማንም ቢኖር፥ ይህን ተመልከቱት፥ ያፍርም ዘንድ ከእርሱ ጋር አትተባበሩ።
14and if any one do not obey our word through the letter, this one note ye, and have no company with him, that he may be ashamed,
15ነገር ግን እንደ ወንድም ገሥጹት እንጂ እንደ ጠላት አትቍጠሩት።
15and as an enemy count [him] not, but admonish ye [him] as a brother;
16የሰላምም ጌታ ራሱ በሁሉ መንገድ ዘወትር ሰላምን ይስጣችሁ። ጌታ ከሁላችሁ ጋር ይሁን።
16and may the Lord of the peace Himself give to you the peace always in every way; the Lord [is] with you all!
17በገዛ እጄ የተጻፈ የእኔ የጳውሎስ ሰላምታ ይህ ነው፤ የመልእክቴ ሁሉ ማስረጃ ይህ ነው፤ እንዲህ እጽፋለሁ።
17The salutation by the hand of me, Paul, which is a sign in every letter; thus I write;
18የጌታችን የኢየሱስ ክርስቶስ ጸጋ ከሁላችሁ ጋር ይሁን።
18the grace of our Lord Jesus Christ [is] with you all! Amen.