Young`s Literal Translation

Amharic: New Testament

2 Timothy

2

1Thou, therefore, my child, be strong in the grace that [is] in Christ Jesus,
1እንግዲህ፥ ልጄ ሆይ፥ አንተ በክርስቶስ ኢየሱስ ባለው ጸጋ በርታ።
2and the things that thou didst hear from me through many witnesses, these things be committing to stedfast men, who shall be sufficient also others to teach;
2ብዙ ሰዎች የመሰከሩለትን ከእኔም የሰማኸውን ሌሎችን ደግሞ ሊያስተምሩ ለሚችሉ ለታመኑ ሰዎች አደራ ስጥ።
3thou, therefore, suffer evil as a good soldier of Jesus Christ;
3እንደ ኢየሱስ ክርስቶስ በጎ ወታደር ሆነህ፥ አብረኸኝ መከራ ተቀበል።
4no one serving as a soldier did entangle himself with the affairs of life, that him who did enlist him he may please;
4የሚዘምተው ሁሉ ለጦር ያስከተተውን ደስ ያሰኝ ዘንድ ትዳር በሚገኝበት ንግድ ራሱን አያጠላልፍም።
5and if also any one may strive, he is not crowned, except he may strive lawfully;
5ደግሞም በጨዋታ የሚታገል ማንም ቢሆን፥ እንደሚገባ አድርጎ ባይታገል፥ የድሉን አክሊል አያገኝም።
6the labouring husbandman it behoveth first of the fruits to partake;
6የሚደክመው ገበሬ ፍሬውን ከሚበሉት መጀመሪያ እንዲሆን ይገባዋል።
7be considering what things I say, for the Lord give to thee understanding in all things.
7የምለውን ተመልከት፤ ጌታም በነገር ሁሉ ማስተዋልን ይስጥህ።
8Remember Jesus Christ, raised out of the dead, of the seed of David, according to my good news,
8በወንጌል እንደምሰብከው፥ ከሙታን የተነሣውን፥ ከዳዊት ዘርም የሆነውን ኢየሱስ ክርስቶስን አስብ፤
9in which I suffer evil -- unto bonds, as an evil-doer, but the word of God hath not been bound;
9ይህንም በመስበክ እንደ ክፉ አድራጊ እስክታሰር ድረስ መከራ እቀበላለሁ፥ የእግዚአብሔር ቃል ግን አይታሰርም።
10because of this all things do I endure, because of the choice ones, that they also salvation may obtain that [is] in Christ Jesus, with glory age-during.
10ስለዚህ እነርሱ ደግሞ በክርስቶስ ኢየሱስ ያለውን መዳን ከዘላለም ክብር ጋር እንዲያገኙ ስለ ተመረጡት በነገር ሁሉ እጸናለሁ።
11Stedfast [is] the word: For if we died together -- we also shall live together;
11ቃሉ የታመነ ነው እንዲህ የሚለው። ከእርሱ ጋር ከሞትን፥ ከእርሱ ጋር ደግሞ በሕይወት እንኖራለን፤
12if we do endure together -- we shall also reign together; if we deny [him], he also shall deny us;
12ብንጸና፥ ከእርሱ ጋር ደግሞ እንነግሣለን፤ ብንክደው፥ እርሱ ደግሞ ይክደናል፤
13if we are not stedfast, he remaineth stedfast; to deny himself he is not able.
13ባናምነው፥ እርሱ የታመነ ሆኖ ይኖራል፤ ራሱን ሊክድ አይችልምና።
14These things remind [them] of, testifying fully before the Lord -- not to strive about words to nothing profitable, but to the subversion of those hearing;
14ይህን አሳስባቸው፥ በቃልም እንዳይጣሉ በእግዚአብሔር ፊት ምከራቸው፥ ይህ ምንም የማይረባ የሚሰሙትንም የሚያፈርስ ነውና።
15be diligent to present thyself approved to God -- a workman irreproachable, rightly dividing the word of the truth;
15የእውነትን ቃል በቅንነት የሚናገር የማያሳፍርም ሠራተኛ ሆነህ፥ የተፈተነውን ራስህን ለእግዚአብሔር ልታቀርብ ትጋ።
16and the profane vain talkings stand aloof from, for to more impiety they will advance,
16ነገር ግን ለዓለም ከሚመች ከከንቱ መለፍለፍ ራቅ፤ ኃጢአተኝነታቸውን ከፊት ይልቅ ይጨምራሉና፥ ቃላቸውም እንደ ጭንቁር ይባላል፤
17and their word as a gangrene will have pasture, of whom is Hymenaeus and Philetus,
17ከእነርሱም ሄሜኔዎስና ፊሊጦስ ናቸው፤
18who concerning the truth did swerve, saying the rising again to have already been, and do overthrow the faith of some;
18እነዚህም። ትንሣኤ ከአሁን በፊት ሆኖአል እያሉ፥ ስለ እውነት ስተው፥ የአንዳንዶችን እምነት ይገለብጣሉ።
19sure, nevertheless, hath the foundation of God stood, having this seal, `The Lord hath known those who are His,' and `Let him depart from unrighteousness -- every one who is naming the name of Christ.'
19ሆኖም። ጌታ ለእርሱ የሆኑትን ያውቃል፥ ደግሞም። የጌታን ስም የሚጠራ ሁሉ ከዓመፅ ይራቅ የሚለው ማኅተም ያለበት የተደላደለ የእግዚአብሔር መሠረት ቆሞአል።
20And in a great house there are not only vessels of gold and of silver, but also of wood and of earth, and some to honour, and some to dishonour:
20በትልቅም ቤት የእንጨትና የሸክላ ዕቃ ደግሞ አለ እንጂ የወርቅና የብር ዕቃ ብቻ አይደለም፥ እኵሌቶቹም ለክብር፥ እኵሌቶቹም ለውርደት ይሆናሉ፤
21if, then, any one may cleanse himself from these, he shall be a vessel to honour, sanctified and profitable to the master -- to every good work having been prepared,
21እንግዲህ ማንም ራሱን ከእነዚህ ቢያነጻ፥ ለክብር የሚሆን የተቀደሰም ለጌታውም የሚጠቅም ለበጎም ሥራ ሁሉ የተዘጋጀ ዕቃ ይሆናል።
22and the youthful lusts flee thou, and pursue righteousness, faith, love, peace, with those calling upon the Lord out of a pure heart;
22ከክፉ የጎልማሳነት ምኞት ግን ሽሽ፥ በንጹሕም ልብ ጌታን ከሚጠሩ ጋር ጽድቅን እምነትን ፍቅርን ሰላምን አጥብቀህ ተከተል።
23and the foolish and uninstructed questions be avoiding, having known that they beget strife,
23ነገር ግን ጠብን እንዲያመጣ አውቀህ ከሰነፎችና ካልተማሩ ምርመራ ራቅ፤
24and a servant of the Lord it behoveth not to strive, but to be gentle unto all, apt to teach, patient under evil,
24የጌታም ባሪያ ለሰው ሁሉ ገር ለማስተማርም የሚበቃ ለትዕግሥትም የሚጸና ሊሆን እንጂ ሊጣላ አይገባውም።
25in meekness instructing those opposing -- if perhaps God may give to them repentance to an acknowledging of the truth,
25ደግሞም። ምናልባት እግዚአብሔር እውነትን ያውቁ ዘንድ ንስሐን ይሰጣቸዋልና ፈቃዱን ለማድረግ በዲያብሎስ ሕያዋን ሆነው ከተያዙበት ወጥመድ ወጥተው፥ ወደ አእምሮ ይመለሳሉ ብሎ የሚቃወሙትን በየዋህነት ይቅጣ።
26and they may awake out of the devil's snare, having been caught by him at his will.