1And having passed through Amphipolis, and Apollonia, they came to Thessalonica, where was the synagogue of the Jews,
1በአንፊጶልና በአጶሎንያም ካለፉ በኋላ ወደ ተሰሎንቄ መጡ፥ በዚያም የአይሁድ ምኵራብ ነበረ።
2and according to the custom of Paul, he went in unto them, and for three sabbaths he was reasoning with them from the Writings,
2ጳውሎስም እንደ ልማዱ ወደ እነርሱ ገባ፥ ሦስት ሰንበትም ያህል ከእነርሱ ጋር ከመጻሕፍት እየጠቀሰ ይነጋገር ነበር፤
3opening and alleging, `That the Christ it behoved to suffer, and to rise again out of the dead, and that this is the Christ — Jesus whom I proclaim to you.`
3ሲተረጉምም ክርስቶስ መከራ እንዲቀበልና ከሙታን እንዲነሣ ይገባው ዘንድ እያስረዳ። ይህ እኔ የምሰብክላችሁ ኢየሱስ እርሱ ክርስቶስ ነው ይል ነበር።
4And certain of them did believe, and attached themselves to Paul and to Silas, also of the worshipping Greeks a great multitude, of the principal women also not a few.
4ከእነርሱም አንዳንዶቹ ተረድተው ከሚያመልኩም ከግሪክ ሰዎች ብዙ ከከበሩትም ሴቶች ጥቂቶች ያይደሉ፥ ከጳውሎስና ከሲላስ ጋር ተባበሩ።
5And the unbelieving Jews, having been moved with envy, and having taken to them of the loungers certain evil men, and having made a crowd, were setting the city in an uproar; having assailed also the house of Jason, they were seeking them to bring [them] to the populace,
5አይሁድ ግን ቀንተው ከሥራ ፈቶች ክፉ ሰዎችን አመጡ ሕዝብንም ሰብስበው ከተማውን አወኩ፥ ወደ ሕዝብም ያወጡአቸው ዘንድ ፈልገው ወደ ኢያሶን ቤት ቀረቡ፤
6and not having found them, they drew Jason and certain brethren unto the city rulers, calling aloud — `These, having put the world in commotion, are also here present,
6ባላገኙአቸውም ጊዜ ኢያሶንንና ከወንድሞች አንዳንዶችን ወደ ከተማው አለቆች ጎትተው። ዓለምን ያወኩ እነዚህ ወደዚህ ደግሞ መጥተዋል፥ ኢያሶንም ተቀብሎአቸዋል፤
7whom Jason hath received; and these all do contrary to the decrees of Caesar, saying another to be king — Jesus.`
7እነዚህም ሁሉ። ኢየሱስ የሚሉት ሌላ ንጉሥ አለ እያሉ የቄሣርን ትእዛዝ ይቃወማሉ ብለው ጮኹ።
8And they troubled the multitude and the city rulers, hearing these things,
8ሕዝቡና የከተማውም አለቆች ይህን ነገር በሰሙ ጊዜ ታወኩ፥
9and having taking security from Jason and the rest, they let them go.
9ከኢያሶንና ከሌሎቹም ዋስ ተቀብለው ለቀቁአቸው።
10And the brethren immediately, through the night, sent forth both Paul and Silas to Berea, who having come, went to the synagogue of the Jews;
10ወዲያውም ወንድሞች ጳውሎስንና ሲላስን በሌሊት ወደ ቤርያ ሰደዱአቸው፥ በደረሱም ጊዜ ወደ አይሁድ ምኵራብ ገቡ፤
11and these were more noble than those in Thessalonica, they received the word with all readiness of mind, every day examining the Writings whether those things were so;
11እነዚህም በተሰሎንቄ ከሚኖሩት ይልቅ ልበ ሰፊዎች ነበሩና። ነገሩ እንደዚሁ ይሆንን? ብለው ዕለት ዕለት መጻሕፍትን እየመረመሩ ቃሉን በሙሉ ፈቃድ ተቀበሉ።
12many, indeed, therefore, of them did believe, and of the honourable Greek women and men not a few.
12ስለዚህም ከእነርሱ ብዙ፥ ከግሪኮችም የከበሩት ሴቶችና ወንዶች ጥቂት ያይደሉ፥ አመኑ።
13And when the Jews from Thessalonica knew that also in Berea was the word of God declared by Paul, they came thither also, agitating the multitudes;
13በተሰሎንቄ ያሉት አይሁድ ግን ጳውሎስ በቤርያ ደግሞ የእግዚአብሔርን ቃል እንደ ሰበከ ባወቁ ጊዜ፥ ወደዚያው ደግሞ መጡና ሕዝቡን አወኩ።
14and then immediately the brethren sent forth Paul, to go on as it were to the sea, but both Silas and Timothy were remaining there.
14በዚያን ጊዜም ወንድሞቹ ወዲያው ጳውሎስን እስከ ባሕር ድረስ ይሄድ ዘንድ ሰደዱት፤ ሲላስና ጢሞቴዎስም በዚያው ቀሩ።
15And those conducting Paul, brought him unto Athens, and having received a command unto Silas and Timotheus that with all speed they may come unto him, they departed;
15ጳውሎስን የሸኙት ግን እስከ አቴና አደረሱት፥ እንደሚቻላቸውም በፍጥነት ወደ እርሱ ይመጡ ዘንድ ወደ ሲላስና ወደ ጢሞቴዎስ ትእዛዝ ተቀብለው ሄዱ።
16and Paul waiting for them in Athens, his spirit was stirred in him, beholding the city wholly given to idolatry,
16ጳውሎስም በአቴና ሲጠብቃቸው ሳለ፥ በከተማው ጣዖት መሙላቱን እየተመለከተ መንፈሱ ተበሳጨበት።
17therefore, indeed, he was reasoning in the synagogue with the Jews, and with the worshipping persons, and in the market-place every day with those who met with him.
17ስለዚህም በምኵራብ ከአይሁድና እግዚአብሔርን ከሚያመልኩ ሰዎች ጋር በየቀኑም በገበያ ከሚያገኛቸው ጋር ይነጋገር ነበር።
18And certain of the Epicurean and of the Stoic philosophers, were meeting together to see him, and some were saying, `What would this seed picker wish to say?` and others, `Of strange demons he doth seem to be an announcer;` because Jesus and the rising again he did proclaim to them as good news,
18ከኤፊቆሮስ ወገንና ኢስጦኢኮችም ከተባሉት ፈላስፎች አንዳንዶቹ ከእርሱ ጋር ተገናኙ። አንዳንዶቹም። ይህ ለፍላፊ ምን ሊናገር ይወዳል? አሉ፤ ሌሎችም የኢየሱስንና የትንሣኤውን ወንጌል ስለ ሰበከላቸው። አዲሶችን አማልክት የሚያወራ ይመስላል አሉ።
19having also taken him, unto the Areopagus they brought [him], saying, `Are we able to know what [is] this new teaching that is spoken by thee,
19ይዘውም። ይህ የምትናገረው አዲስ ትምህርት ምን እንደሆነ እናውቅ ዘንድ ይቻለናልን? በጆሮአችን እንግዳ ነገር ታሰማናለህና፤ እንግዲህ ይህ ነገር ምን እንደሆነ እናውቅ ዘንድ እንፈቅዳለን ብለው አርዮስፋጎስ ወደ ተባለው ስፍራ ወሰዱት።
20for certain strange things thou dost bring to our ears? we wish, then, to know what these things would wish to be;`
21የአቴና ሰዎች ሁሉና በዚያ የኖሩ እንግዶች አዲስ ነገርን ከመናገርና ከመስማት በቀር በሌላ ጉዳይ አይውሉም ነበርና።
21and all Athenians, and the strangers sojourning, for nothing else were at leisure but to say something, and to hear some newer thing.
22ጳውሎስም በአርዮስፋጎስ መካከል ቆሞ እንዲህ አለ። የአቴና ሰዎች ሆይ፥ እናንተ በሁሉ ነገር አማልክትን እጅግ እንደምትፈሩ እመለከታለሁ።
22And Paul, having stood in the midst of the Areopagus, said, `Men, Athenians, in all things I perceive you as over-religious;
23የምታመልኩትን እየተመለከትሁ ሳልፍ። ለማይታወቅ አምላክ የሚል ጽሕፈት ያለበትን መሠዊያ ደግሞ አግኝቼአለሁና። እንግዲህ ይህን ሳታውቁ የምታመልኩትን እኔ እነግራችኋለሁ።
23for passing through and contemplating your objects of worship, I found also an erection on which had been inscribed: To God — unknown; whom, therefore — not knowing — ye do worship, this One I announce to you.
24ዓለሙንና በእርሱ ያለውን ሁሉ የፈጠረ አምላክ እርሱ የሰማይና የምድር ጌታ ነውና እጅ በሠራው መቅደስ አይኖርም፤
24`God, who did make the world, and all things in it, this One, of heaven and of earth being Lord, in temples made with hands doth not dwell,
25እርሱም ሕይወትንና እስትንፋስን ሁሉንም ለሁሉ ይሰጣልና አንዳች እንደሚጎድለው በሰው እጅ አይገለገልም።
25neither by the hands of men is He served — needing anything, He giving to all life, and breath, and all things;
26ምናልባትም እየመረመሩ ያገኙት እንደ ሆነ፥ እግዚአብሔርን ይፈልጉ ዘንድ በምድር ሁሉ ላይ እንዲኖሩ የሰውን ወገኖች ሁሉ ከአንድ ፈጠረ፥ የተወሰኑትንም ዘመኖችና ለሚኖሩበት ስፍራ ዳርቻ መደበላቸው። ቢሆንም ከእያንዳንዳችን የራቀ አይደለም።
26He made also of one blood every nation of men, to dwell upon all the face of the earth — having ordained times before appointed, and the bounds of their dwellings —
28ከእናንተ ከባለ ቅኔዎች አንዳንዶች ደግሞ። እኛ ደግሞ ዘመዶቹ ነንና ብለው እንደ ተናገሩ፥ በእርሱ ሕያዋን ነንና እንንቀሳቀሳለን እንኖርማለን።
27to seek the Lord, if perhaps they did feel after Him and find, — though, indeed, He is not far from each one of us,
29እንግዲህ የእግዚአብሔር ዘመዶች ከሆንን፥ አምላክ በሰው ብልሃትና አሳብ የተቀረጸውን ወርቅ ወይም ብር ወይም ድንጋይ እንዲመስል እናስብ ዘንድ አይገባንም።
28for in Him we live, and move, and are; as also certain of your poets have said: For of Him also we are offspring.
30እንግዲህ እግዚአብሔር ያለማወቅን ወራት አሳልፎ አሁን በየቦታቸው ንስሐ ይገቡ ዘንድ ሰውን ሁሉ ያዛል፤
29`Being, therefore, offspring of God, we ought not to think the Godhead to be like to gold, or silver, or stone, graving of art and device of man;
31ቀን ቀጥሮአልና፥ በዚያም ቀን ባዘጋጀው ሰው እጅ በዓለሙ ላይ በጽድቅ ሊፈርድ አለው፤ ስለዚህም እርሱን ከሙታን በማስነሣቱ ሁሉን አረጋግጦአል።
30the times, indeed, therefore, of the ignorance God having overlooked, doth now command all men everywhere to reform,
32የሙታንንም ትንሣኤ በሰሙ ጊዜ እኵሌቶቹ አፌዙበት፥ እኵሌቶቹ ግን። ስለዚህ ነገር ሁለተኛ እንሰማሃለን አሉት።
31because He did set a day in which He is about to judge the world in righteousness, by a man whom He did ordain, having given assurance to all, having raised him out of the dead.`
33እንዲሁም ጳውሎስ ከመካከላቸው ወጣ።
32And having heard of a rising again of the dead, some, indeed, were mocking, but others said, `We will hear thee again concerning this;`
34አንዳንዶች ወንዶች ግን ተባብረው አመኑ፤ ከእነርሱ ደግሞ በአርዮስፋጎስ ያለው የፍርድ ቤት ፈራጅ ዲዮናስዮስ ደማሪስ የሚሉአትም አንዲት ሴት ሌሎችም ከእነርሱ ጋር ነበሩ።
33and so Paul went forth from the midst of them,
34and certain men having cleaved to him, did believe, among whom [is] also Dionysius the Areopagite, and a woman, by name Damaris, and others with them.