Young`s Literal Translation

Amharic: New Testament

Acts

19

1And it came to pass, in Apollos` being in Corinth, Paul having gone through the upper parts, came to Ephesus, and having found certain disciples,
1አጵሎስም በቆሮንቶስ ሳለ ጳውሎስ በላይኛው አገር አልፎ ወደ ኤፌሶን መጣ፥
2he said unto them, `The Holy Spirit did ye receive — having believed?` and they said unto him, `But we did not even hear whether there is any Holy Spirit;`
2አንዳንድ ደቀ መዛሙርትንም አገኘ። ባመናችሁ ጊዜ መንፈስ ቅዱስን ተቀበላችሁን? አላቸው። እነርሱም። አልተቀበልንም መንፈስ ቅዱስ እንዳለ ስንኳ አልሰማንም አሉት።
3and he said unto them, `To what, then, were ye baptized?` and they said, `To John`s baptism.`
3እንኪያ በምን ተጠመቃችሁ? አላቸው። እነርሱም። በዮሐንስ ጥምቀት አሉት።
4And Paul said, `John, indeed, did baptize with a baptism of reformation, saying to the people that in him who is coming after him they should believe — that is, in the Christ — Jesus;`
4ጳውሎስም። ዮሐንስስ ከእርሱ በኋላ በሚመጣው በኢየሱስ ክርስቶስ ያምኑ ዘንድ ለሕዝብ እየተናገረ በንስሐ ጥምቀት አጠመቀ አላቸው።
5and they, having heard, were baptized — to the name of the Lord Jesus,
5ይህንም በሰሙ ጊዜ በጌታ በኢየሱስ ስም ተጠመቁ፤
6and Paul having laid on them [his] hands, the Holy Spirit came upon them, they were speaking also with tongues, and prophesying,
6ጳውሎስም እጁን በጫነባቸው ጊዜ መንፈስ ቅዱስ ወረደባቸው በልሳኖችም ተናገሩ፥ ትንቢትም ተናገሩ።
7and all the men were, as it were, twelve.
7ሰዎቹም ሁሉ አሥራ ሁለት ያህሉ ነበር።
8And having gone into the synagogue, he was speaking boldly for three months, reasoning and persuading the things concerning the reign of God,
8ወደ ምኵራብም ገብቶ ስለ እግዚአብሔር መንግሥት እየተነጋገረና እያስረዳቸው ሦስት ወር ያህል በግልጥ ይናገር ነበር።
9and when certain were hardened and were disbelieving, speaking evil of the way before the multitude, having departed from them, he did separate the disciples, every day reasoning in the school of a certain Tyrannus.
9አንዳንዶች ግን እልከኞች ሆነው በሕዝብ ፊት መንገዱን እየሰደቡ ባላመኑ ጊዜ፥ ከእነርሱ ርቆ ደቀ መዛሙርትን ለየ፥ ጢራኖስም በሚሉት በትምህርት ቤት ዕለት ዕለት ይነጋገር ነበር።
10And this happened for two years so that all those dwelling in Asia did hear the word of the Lord Jesus, both Jews and Greeks,
10በእስያም የኖሩት ሁሉ አይሁድም የግሪክ ሰዎችም የጌታን ቃል እስኪሰሙ ድረስ ሁለት ዓመት ያህል እንዲህ ሆነ።
11mighty works also — not common — was God working through the hands of Paul,
11እግዚአብሔርም በጳውሎስ እጅ የሚያስገርም ተአምራት ያደርግ ነበር፤ ስለዚህም ከአካሉ ጨርቅ ወይም ልብስ ወደ ድውዮች ይወስዱ ነበር፥
12so that even unto the ailing were brought from his body handkerchiefs or aprons, and the sicknesses departed from them; the evil spirits also went forth from them.
12ደዌያቸውም ይለቃቸው ነበር ክፉዎች መናፍስትም ይወጡ ነበር።
13And certain of the wandering exorcist Jews, took upon [them] to name over those having the evil spirits the name of the Lord Jesus, saying, `We adjure you by Jesus, whom Paul doth preach;`
13አጋንንትንም እያወጡ ይዞሩ ከነበሩት አይሁድ አንዳንዶች። ጳውሎስ በሚሰብከው በኢየሱስ እናምላችኋለን እያሉ ክፉዎች መናፍስት ባሉባቸው ላይ የጌታን የኢየሱስን ስም ይጠሩባቸው ዘንድ ሞከሩ።
14and there were certain — seven sons of Sceva, a Jew, a chief priest — who are doing this thing;
14የካህናትም አለቃ ለሆነ አስቄዋ ለሚሉት ለአንድ አይሁዳዊ ይህን ያደረጉ ሰባት ልጆች ነበሩት።
15and the evil spirit, answering, said, `Jesus I know, and Paul I am acquainted with; and ye — who are ye?`
15ክፉው መንፈስ ግን መልሶ። ኢየሱስንስ አውቀዋለሁ ጳውሎስንም አውቀዋለሁ፤ እናንተሳ እነማን ናችሁ? አላቸው።
16And the man, in whom was the evil spirit, leaping upon them, and having overcome them, prevailed against them, so that naked and wounded they did flee out of that house,
16ክፉው መንፈስም ያለበት ሰው ዘለለባቸው ቆስለውም ከዚያ ቤት ዕራቁታቸውን እስኪሸሹ ድረስ በረታባቸው አሸነፋቸውም።
17and this became known to all, both Jews and Greeks, who are dwelling at Ephesus, and fear fell upon them all, and the name of the Lord Jesus was being magnified,
17ይህም በኤፌሶን በሚኖሩት ሁሉ በአይሁድና በግሪክ ሰዎች ዘንድ የታወቀ ሆነ፥ በሁላቸውም ላይ ፍርሃት ወደቀባቸው፥ የጌታም የኢየሱስ ስም ተከበረ፤
18many also of those who did believe were coming, confessing and declaring their acts,
18አምነውም ከነበሩት እጅግ ሰዎች ያደረጉትን እየተናዘዙና እየተናገሩ ይመጡ ነበር።
19and many of those who had practised the curious arts, having brought the books together, were burning [them] before all; and they reckoned together the prices of them, and found [it] five myriads of silverlings;
19ከአስማተኞችም ብዙዎቹ መጽሐፋቸውን ሰብስበው በሰው ሁሉ ፊት አቃጠሉት፤ ዋጋውም ቢታሰብ አምሳ ሺህ ብር ሆኖ ተገኘ።
20so powerfully was the word of God increasing and prevailing.
20እንዲህም የጌታ ቃል በኃይል ያድግና ያሸንፍ ነበር።
21And when these things were fulfilled, Paul purposed in the Spirit, having gone through Macedonia and Achaia, to go on to Jerusalem, saying — `After my being there, it behoveth me also to see Rome;`
21ይህም በተፈጸመ ጊዜ ጳውሎስ። ወደዚያ ደርሼ ሮሜን ደግሞ አይ ዘንድ ይገባኛል ብሎ በመቄዶንያና በአካይያ አልፎ ወደ ኢየሩሳሌም እንዲሄድ በመንፈስ አሰበ።
22and having sent to Macedonia two of those ministering to him — Timotheus and Erastus — he himself stayed a time in Asia.
22ከሚያገለግሉትም ሁለቱን ጢሞቴዎስንና ኤርስጦንን ወደ መቄዶንያ ልኮ ራሱ በእስያ ጥቂት ቀን ቆየ።
23And there came, at that time, not a little stir about the way,
23በዚያም ጊዜ ስለዚህ መንገድ ብዙ ሁከት ሆነ።
24for a certain one, Demetrius by name, a worker in silver, making silver sanctuaries of Artemis, was bringing to the artificers gain not a little,
24ብር ሠሪ የሆነ ድሜጥሮስ የሚሉት አንድ ሰው የአርጤምስን ቤተ መቅደስ ምስሎች በብር እየሠራ ለአንጥረኞች እጅግ ትርፍ ያገኝ ነበርና፤
25whom, having brought in a crowd together, and those who did work about such things, he said, `Men, ye know that by this work we have our wealth;
25እነዚህንም ይህንም የሚመስለውን ሥራ የሠሩትን ሰብስቦ እንዲህ አላቸው። ሰዎች ሆይ፥ ትርፋችን በዚህ ሥራ እንደ ሆነ ታውቃላችሁ።
26and ye see and hear, that not only at Ephesus, but almost in all Asia, this Paul, having persuaded, did turn away a great multitude, saying, that they are not gods who are made by hands;
26ይህም ጳውሎስ። በእጅ የተሠሩቱ አማልክት አይደሉም ብሎ፥ በኤፌሶን ብቻ ሳይሆን ከጥቂት ክፍል በቀር በእስያ ሁሉ ብዙ ሕዝብን እንደ አስረዳና እንደ አሳተ አይታችኋል ሰምታችሁማል።
27and not only is this department in danger for us of coming into disregard, but also, that of the great goddess Artemis the temple is to be reckoned for nothing, and also her greatness is about to be brought down, whom all Asia and the world doth worship.`
27ሥራችንም እንዲናቅ ብቻ አይደለም፥ እስያ ሁሉ ዓለሙም የሚያመልካት የታላቂቱ አምላክ የአርጤምስ መቅደስ ምናምን ሆኖ እንዲቆጠር እንጂ፥ ታላቅነትዋም ደግሞ እንዳይሻር ያስፈራል።
28And they having heard, and having become full of wrath, were crying out, saying, `Great [is] the Artemis of the Ephesians!`
28ይህንም በሰሙ ጊዜ ቍጣ ሞላባቸው። የኤፌሶን አርጤምስ ታላቅ ናት እያሉም ጮኹ።
29and the whole city was filled with confusion, they rushed also with one accord into the theatre, having caught Gaius and Aristarchus, Macedonians, Paul`s fellow-travellers.
29ከተማውም በሙሉው ተደባለቀ፥ የመቄዶንያም ሰዎች የጳውሎስን ጓደኞች ጋይዮስንና አርስጥሮኮስን ከእነርሱ ጋር ነጥቀው በአንድ ልብ ሆነው ወደ ጨዋታ ስፍራ ሮጡ።
30And on Paul`s purposing to enter in unto the populace, the disciples were not suffering him,
30ጳውሎስም ወደ ሕዝቡ ይገባ ዘንድ በፈቀደ ጊዜ ደቀ መዛሙርት ከለከሉት።
31and certain also of the chief men of Asia, being his friends, having sent unto him, were entreating him not to venture himself into the theatre.
31ከእስያም አለቆች ወዳጆቹ የሆኑት አንዳንዶች ደግሞ ወደ እርሱ ልከው ወደ ጨዋታ ስፍራ ራሱን እንዳይሰጥ ለመኑት።
32Some indeed, therefore, were calling out one thing, and some another, for the assembly was confused, and the greater part did not know for what they were come together;
32ወዲያና ወዲህም እያሉ ይጮኹ ነበር፤ በጉባኤው ድብልቅልቅ ሆኖ የሚበልጡት ስንኳ ስለ ምን እንደተሰበሰቡ አላወቁም ነበርና።
33and out of the multitude they put forward Alexander — the Jews thrusting him forward — and Alexander having beckoned with the hand, wished to make defence to the populace,
33አይሁድም ሲያቀርቡት፥ እስክንድሮስን ከሕዝቡ መካከል ወደ ፊት ገፉት፤ እስክንድሮስም በእጁ ጠቅሶ በሕዝብ ፊት እንዲምዋገትላቸው ወደደ።
34and having known that he is a Jew, one voice came out of all, for about two hours, crying, `Great [is] the Artemis of the Ephesians!`
34አይሁዳዊ ግን እንደ ሆነ ባወቁ ጊዜ፥ ሁሉ በአንድ ድምፅ። የኤፌሶን አርጤምስ ታላቅ ናት እያሉ ሁለት ሰዓት ያህል ጮኹ።
35And the public clerk having quieted the multitude, saith, `Men, Ephesians, why, who is the man that doth not know that the city of the Ephesians is a devotee of the great goddess Artemis, and of that which fell down from Zeus?
35የከተማይቱም ጸሐፊ ሕዝቡን ጸጥ አሰኝቶ እንዲህ አለ። የኤፌሶን ሰዎች ሆይ፥ የኤፌሶን ከተማ ለታላቂቱ አርጤምስ ከሰማይም ለወረደው ጣዖትዋ የመቅደስ ጠባቂ መሆንዋን የማያውቅ ሰው ማን ነው?
36these things, then, not being to be gainsaid, it is necessary for you to be quiet, and to do nothing rashly.
36ይህንም የሚክደው ከሌለ፥ ጸጥ እንድትሉና አንዳች በችኮላ እንዳታደርጉ ይገባል።
37`For ye brought these men, who are neither temple-robbers nor speaking evil of your goddess;
37የመቅደስን ዕቃ ያልሰረቁ አምላካችንንም ያልሰደቡ እነዚህን ሰዎች አምጥታችኋቸዋልና።
38if indeed, therefore, Demetrius and the artificers with him with any one have a matter, court [days] are held, and there are proconsuls; let them accuse one another.
38ድሜጥሮስና ከእርሱ ጋር ያሉት አንጥረኞች ግን በሰው ላይ ነገር እንዳላቸው፥ የመጋቢያ ቀንና አገረ ገዢዎች አሉ፤ እርስ በርሳቸው ይምዋገቱ።
39`And if ye seek after anything concerning other matters, in the legal assembly it shall be determined;
39ስለ ሌላ ነገር እንደ ሆነ ግን አንዳች ብትፈልጉ፥ በተደነገገው ጉባኤ ይፈታል።
40for we are also in peril of being accused of insurrection in regard to this day, there being no occasion by which we shall be able to give an account of this concourse;`
40ዛሬ ስለ ተደረገው። ሁከት ነው ሲሉ እንዳይከሱን ያስፈራልና፤ ስለዚህም ስብሰባ ምላሽ መስጠት አንችልም፥ ምክንያት የለምና።
41and these things having said, he dismissed the assembly.
41ይህንም ብሎ ጉባኤውን ፈታው።