Young`s Literal Translation

Amharic: New Testament

Colossians

2

1For I wish you to know how great a conflict I have for you and those in Laodicea, and as many as have not seen my face in the flesh,
1ስለ እናንተና በሎዶቅያ ስላሉት ፊቴንም በሥጋ ስላላዩት ሁሉ እንዴት ያለ ትልቅ መጋደል እንዳለኝ ልታውቁ እወዳለሁና።
2that their hearts may be comforted, being united in love, and to all riches of the full assurance of the understanding, to the full knowledge of the secret of the God and Father, and of the Christ,
2ልባቸው እንዲጸናና፥ በፍቅርም ተባብረው በማስተዋል ወደሚገኝበት ወደ መረዳት ባለ ጠግነት ሁሉ እንዲደርሱ የእግዚአብሔርንም ምሥጢር እርሱንም ክርስቶስን እንዲያውቁ እጋደላለሁ።
3in whom are all the treasures of the wisdom and the knowledge hid,
3የተሰወረ የጥበብና የእውቀት መዝገብ ሁሉ በእርሱ ነውና።
4and this I say, that no one may beguile you in enticing words,
4ማንም በሚያባብል ቃል እንዳያስታችሁ ይህን እላለሁ።
5for if even in the flesh I am absent — yet in the spirit I am with you, joying and beholding your order, and the stedfastness of your faith in regard to Christ;
5በሥጋ ምንም እንኳ ብርቅ፥ በመንፈስ ከእናንተ ጋር ነኝና፥ ሥርዓታችሁንም በክርስቶስም ያለውን የእምነታችሁን ጽናት እያየሁ ደስ ይለኛል።
6as, then, ye did receive Christ Jesus the Lord, in him walk ye,
6እንግዲህ ጌታን ክርስቶስ ኢየሱስን እንደ ተቀበላችሁት በእርሱ ተመላለሱ።
7being rooted and built up in him, and confirmed in the faith, as ye were taught — abounding in it in thanksgiving.
7ሥር ሰዳችሁ በእርሱ ታነጹ፥ እንደ ተማራችሁም በሃይማኖት ጽኑ፥ ምስጋናም ይብዛላችሁ።
8See that no one shall be carrying you away as spoil through the philosophy and vain deceit, according to the deliverance of men, according to the rudiments of the world, and not according to Christ,
8እንደ ክርስቶስ ትምህርት ሳይሆን፥ እንደ ሰው ወግና እንደ ዓለማዊ እንደ መጀመሪያ ትምህርት ባለ በፍልስፍና በከንቱም መታለል ማንም እንዳይማርካችሁ ተጠበቁ።
9because in him doth tabernacle all the fulness of the Godhead bodily,
9በእርሱ የመለኮት ሙላት ሁሉ በሰውነት ተገልጦ ይኖራልና።
10and ye are in him made full, who is the head of all principality and authority,
10ለአለቅነትና ለሥልጣንም ሁሉ ራስ በሆነ በእርሱ ሆናችሁ ተሞልታችኋል።
11in whom also ye were circumcised with a circumcision not made with hands, in the putting off of the body of the sins of the flesh in the circumcision of the Christ,
11የሥጋንም ሰውነት በመገፈፍ፥ በክርስቶስ መገረዝ፥ በእጅ ባልተደረገ መገረዝ በእርሱ ሆናችሁ ደግሞ ተገረዛችሁ።
12being buried with him in the baptism, in which also ye rose with [him] through the faith of the working of God, who did raise him out of the dead.
12በጥምቀትም ከእርሱ ጋር ተቀብራችሁ፥ በጥምቀት ደግሞ፥ ከሙታን ባስነሣው በእግዚአብሔር አሠራር በማመናችሁ፥ ከእርሱ ጋር ተነሣችሁ።
13And you — being dead in the trespasses and the uncircumcision of your flesh — He made alive together with him, having forgiven you all the trespasses,
13እናንተም በበደላችሁና ሥጋችሁን ባለመገረዝ ሙታን በሆናችሁ ጊዜ፥ ከእርሱ ጋር ሕይወትን ሰጣችሁ። በደላችሁን ሁሉ ይቅር አላችሁ።
14having blotted out the handwriting in the ordinances that is against us, that was contrary to us, and he hath taken it out of the way, having nailed it to the cross;
14በእኛ ላይ የነበረውን የሚቃወመንንም በትእዛዛት የተጻፈውን የዕዳ ጽሕፈት ደመሰሰው። እርሱንም በመስቀል ጠርቆ ከመንገድ አስወግዶታል።
15having stripped the principalities and the authorities, he made a shew of them openly — having triumphed over them in it.
15አለቅነትንና ሥልጣናትን ገፎ፥ ድል በመንሣት በእርሱ እያዞራቸው በግልጥ አሳያቸው።
16Let no one, then, judge you in eating or in drinking, or in respect of a feast, or of a new moon, or of sabbaths,
16እንግዲህ በመብል ወይም በመጠጥ ወይም ስለ በዓል ወይም ስለ ወር መባቻ ወይም ስለ ሰንበት ማንም አይፍረድባችሁ።
17which are a shadow of the coming things, and the body [is] of the Christ;
17እነዚህ ሊመጡ ያሉት ነገሮች ጥላ ናቸውና፥ አካሉ ግን የክርስቶስ ነው።
18let no one beguile you of your prize, delighting in humble-mindedness and [in] worship of the messengers, intruding into the things he hath not seen, being vainly puffed up by the mind of his flesh,
18ትሕትናንና የመላእክትን አምልኮ እየወደደ፥ ባላየውም ያለ ፈቃድ እየገባ፥ በሥጋዊም አእምሮ በከንቱ እየታበየ ማንም አይፍረድባችሁ።
19and not holding the head, from which all the body — through the joints and bands gathering supply, and being knit together — may increase with the increase of God.
19እንደዚህ ያለ ሰው ራስ ወደሚሆነው አይጠጋም፥ ከእርሱም አካል ሁሉ በጅማትና በማሰሪያ ምግብን እየተቀበለ እየተጋጠመም፥ እግዚአብሔር በሚሰጠው ማደግ ያድጋል።
20If, then, ye did die with the Christ from the rudiments of the world, why, as living in the world, are ye subject to ordinances?
20ከዓለማዊ ከመጀመሪያ ትምህርት ርቃችሁ ከክርስቶስ ጋር ከሞታችሁ፥
21— thou mayest not touch, nor taste, nor handle —
22እንደ ሰው ሥርዓትና ትምህርት። አትያዝ፥ አትቅመስ፥ አትንካ ለሚሉት ትእዛዛት በዓለም እንደምትኖሩ ስለ ምን ትገዛላችሁ? እነዚህ ሁሉ በመደረግ ሊጠፉ ተወስነዋልና።
22which are all for destruction with the using, after the commands and teachings of men,
23ይህ እንደ ገዛ ፈቃድህ በማምለክና በትሕትና ሥጋንም በመጨቆን ጥበብ ያለው ይመስላል፥ ነገር ግን ሥጋ ያለ ልክ እንዳይጠግብ ለመከልከል ምንም አይጠቅምም።
23which are, indeed, having a matter of wisdom in will-worship, and humble-mindedness, and neglecting of body — not in any honour, unto a satisfying of the flesh.