Young`s Literal Translation

Amharic: New Testament

Colossians

4

1The masters! that which is righteous and equal to the servants give ye, having known that ye also have a Master in the heavens.
1ጌቶች ሆይ፥ እናንተ ደግሞ በሰማይ ጌታ እንዳላችሁ ታውቃላችሁና ለባሪያዎቻችሁ በጽድቅና በቅንነት አድርጉላቸው።
2In the prayer continue ye, watching in it in thanksgiving;
2ከማመስገን ጋር በጸሎት እየነቃችሁ ለእርሱ ትጉ።
3praying at the same time also for us, that God may open to us a door for the word, to speak the secret of the Christ, because of which also I have been bound,
3በዚያን ጊዜም ስለ እርሱ ደግሞ የታሰርሁበትን የክርስቶስን ምሥጢር እንድንነግር እግዚአብሔር የቃሉን ደጅ ይከፍትልን ዘንድ ስለ እኛ ደግሞ ጸልዩ።
4that I may manifest it, as it behoveth me to speak;
4ልናገር እንደሚገባኝ ያህል እገልጠው ዘንድ ጸልዩልኝ።
5in wisdom walk ye toward those without, the time forestalling;
5ዘመኑን እየዋጃችሁ፥ በውጭ ባሉቱ ዘንድ በጥበብ ተመላለሱ።
6your word always in grace — with salt being seasoned — to know how it behoveth you to answer each one.
6ለእያንዳንዱ እንዴት እንድትመልሱ እንደሚገባችሁ ታውቁ ዘንድ ንግግራችሁ ሁልጊዜ፥ በጨው እንደ ተቀመመ፥ በጸጋ ይሁን።
7All the things concerning me make known to you shall Tychicus — the beloved brother, and faithful ministrant, and fellow-servant in the Lord —
7የተወደደ ወንድምና የታመነ አገልጋይ በጌታም አብሮኝ ባሪያ የሆነ ቲኪቆስ ኑሮዬን ሁሉ ያስታውቃችኋል።
8whom I did send unto you for this very thing, that he might know the things concerning you, and might comfort your hearts,
8ወሬያችንን እንድታውቁና ልባችሁን እንዲያጽናና፥ ከእናንተ ከሆነውና ከታመነው ከተወደደውም ወንድም ከአናሲሞስ ጋር ወደ እናንተ የምልከው ስለዚህ ምክንያት ነው። የዚህን ስፍራ ወሬ ሁሉ ያስታውቁአችኋል።
9with Onesimus the faithful and beloved brother, who is of you; all things to you shall they make known that [are] here.
10ከተገረዙት ወገን ያሉት፥ አብሮ ከእኔ ጋር የታሰረ አርስጥሮኮስ የበርናባስም የወንድሙ ልጅ ማርቆስ ኢዮስጦስም የተባለ ኢያሱ ሰላምታ ያቀርቡላችኋል። ስለ ማርቆስ። ወደ እናንተ ቢመጣ፥ ተቀበሉት የሚል ትእዛዝ ተቀበላችሁ። በእግዚአብሔር መንግሥት ከእኔ ጋር አብረው የሚሠሩት እነዚህ ብቻ ናቸው፥ እኔንም አጽናንተውኛል።
10Salute you doth Aristarchus, my fellow-captive, and Marcus, the nephew of Barnabas, (concerning whom ye did receive commands — if he may come unto you receive him,)
12ከእናንተ የሆነ የክርስቶስ ባሪያ ኤጳፍራ ሰላምታ ያቀርብላችኋል። በእግዚአብሔር ፈቃድ ሁሉ ተረድታችሁና ፍጹማን ሆናችሁ እንድትቆሙ፥ ሁልጊዜ ስለ እናንተ በጸሎቱ ይጋደላል።
11and Jesus who is called Justus, who are of the circumcision: these only [are] fellow-workers for the reign of God who did become a comfort to me.
13ስለ እናንተ በሎዶቅያም በኢያራ ከተማም ስላሉቱ እጅግ እንዲቀና እመሰክርለታለሁና።
12Salute you doth Epaphras, who [is] of you, a servant of Christ, always striving for you in the prayers, that ye may stand perfect and made full in all the will of God,
14የተወደደው ባለ መድኃኒቱ ሉቃስ ዴማስም ሰላምታ ያቀርቡላችኋል።
13for I do testify to him, that he hath much zeal for you, and those in Laodicea, and those in Hierapolis.
15በሎዶቅያ ላሉቱ ወንድሞችና ለንምፉን በቤቱም ላለች ቤተ ክርስቲያን ሰላምታ አቅርቡልን።
14Salute you doth Lukas, the beloved physician, and Demas;
16ይህችም መልእክት በእናንተ ዘንድ ከተነበበች በኋላ፥ በሎዶቅያ ሰዎች ማኅበር ደግሞ እንድትነበብ አድርጉ። ከሎዶቅያም የምትገኘውን መልእክት እናንተ ደግሞ አንብቡ።
15salute ye those in Laodicea — brethren, and Nymphas, and the assembly in his house;
17ለአክሪጳም። በጌታ የተቀበልኸውን አገልግሎት እንድትፈጽሙው ተጠንቀቅ በሉልኝ።
16and when the epistle may be read with you, cause that also in the assembly of the Laodiceans it may be read, and the [epistle] from Laodicea that ye also may read;
18በገዛ እጄ የተጻፈ የእኔ የጳውሎስ ሰላምታ ይህ ነው። እስራቴን አስቡ። ጸጋ ከእናንተ ጋር ይሁን።
17and say to Archippus, `See to the ministration that thou didst receive in the Lord, that thou mayest fulfil it.`
18The salutation by the hand of me, Paul; remember my bonds; the grace [is] with you. Amen.