1Become, then, followers of God, as children beloved,
1እንግዲህ እንደ ተወደዱ ልጆች እግዚአብሔርን የምትከተሉ ሁኑ፥
2and walk in love, as also the Christ did love us, and did give himself for us, an offering and a sacrifice to God for an odour of a sweet smell,
2ክርስቶስም ደግሞ እንደ ወደዳችሁ ለእግዚአብሔርም የመዓዛ ሽታ የሚሆንን መባንና መሥዋዕትን አድርጎ ስለ እናንተ ራሱን አሳልፎ እንደ ሰጠ በፍቅር ተመላለሱ።
3and whoredom, and all uncleanness, or covetousness, let it not even be named among you, as becometh saints;
3ለቅዱሳን እንደሚገባ ግን ዝሙትና ርኵሰት ሁሉ ወይም መመኘት በእናንተ ዘንድ ከቶ አይሰማ፤
4also filthiness, and foolish talking, or jesting, — the things not fit — but rather thanksgiving;
4የሚያሳፍር ነገርም የስንፍና ንግግርም ወይም ዋዛ የማይገቡ ናቸውና አይሁኑ፥ ይልቁን ምስጋና እንጂ።
5for this ye know, that every whoremonger, or unclean, or covetous person, who is an idolater, hath no inheritance in the reign of the Christ and God.
5ይህን እወቁ፤ አመንዝራም ቢሆን ወይም ርኵስ ወይም የሚመኝ እርሱም ጣዖትን የሚያመልክ በክርስቶስና በእግዚአብሔር መንግሥት ርስት የለውም።
6Let no one deceive you with vain words, for because of these things cometh the anger of God upon the sons of the disobedience,
6ከዚህ የተነሣ በማይታዘዙት ልጆች ላይ የእግዚአብሔር ቁጣ ይመጣልና ማንም በከንቱ ንግግር አያታልላችሁ።
7become not, then, partakers with them,
7እንግዲህ ከእነርሱ ጋር ተካፋዮች አትሁኑ፤
8for ye were once darkness, and now light in the Lord; as children of light walk ye,
8ቀድሞ ጨለማ ነበራችሁና፥ አሁን ግን በጌታ ብርሃን ናችሁ፤
9for the fruit of the Spirit [is] in all goodness, and righteousness, and truth,
9የብርሃኑ ፍሬ በበጎነትና በጽድቅ በእውነትም ሁሉ ነውና ለጌታ ደስ የሚያሰኘውን እየመረመራችሁ፥ እንደ ብርሃን ልጆች ተመላለሱ፤
10proving what is well-pleasing to the Lord,
11ፍሬም ከሌለው ከጨለማ ሥራ ጋር አትተባበሩ፥ ይልቁን ግለጡት እንጂ፥
11and have no fellowship with the unfruitful works of the darkness and rather even convict,
12እነርሱ በስውር ስለሚያደርጉት መናገር እንኳ ነውር ነውና፤
12for the things in secret done by them it is a shame even to speak of,
13ሁሉ ግን በብርሃን ሲገለጥ ይታያል፤ የሚታየው ሁሉ ብርሃን ነውና።
13and all the things reproved by the light are manifested, for everything that is manifested is light;
14ስለዚህ። አንተ የምትተኛ ንቃ ከሙታንም ተነሣ ክርስቶስም ያበራልሃል ይላል።
14wherefore he saith, `Arouse thyself, thou who art sleeping, and arise out of the dead, and the Christ shall shine upon thee.`
15እንግዲህ እንደ ጥበበኞች እንጂ ጥበብ እንደሌላቸው ሳይሆን እንዴት እንድትመላለሱ በጥንቃቄ ተጠበቁ፤
15See, then, how exactly ye walk, not as unwise, but as wise,
16ቀኖቹ ክፉዎች ናቸውና ዘመኑን ዋጁ።
16redeeming the time, because the days are evil;
17ስለዚህ የጌታ ፈቃድ ምን እንደ ሆነ አስተውሉ እንጂ ሞኞች አትሁኑ።
17because of this become not fools, but — understanding what [is] the will of the Lord,
18መንፈስ ይሙላባችሁ እንጂ በወይን ጠጅ አትስከሩ ይህ ማባከን ነውና፤
18and be not drunk with wine, in which is dissoluteness, but be filled in the Spirit,
19በመዝሙርና በዝማሬ በመንፈሳዊም ቅኔ እርስ በርሳችሁ ተነጋገሩ፤ ለጌታ በልባችሁ ተቀኙና ዘምሩ፤
19speaking to yourselves in psalms and hymns and spiritual songs, singing and making melody in your heart to the Lord,
20ሁልጊዜ ስለ ሁሉ በጌታችን በኢየሱስ ክርስቶስ ስም አምላካችንንና አባታችንን ስለ ሁሉ አመስግኑ።
20giving thanks always for all things, in the name of our Lord Jesus Christ, to the God and Father;
21ለእያንዳንዳችሁ በክርስቶስ ፍርሃት የተገዛችሁ ሁኑ።
21subjecting yourselves to one another in the fear of God.
22ሚስቶች ሆይ፥ ለጌታ እንደምትገዙ ለባሎቻችሁ ተገዙ፤
22The wives! to your own husbands subject yourselves, as to the Lord,
23ክርስቶስ ደግሞ የቤተ ክርስቲያን ራስ እንደ ሆነ እርሱም አካሉን የሚያድን እንደ ሆነ ባል የሚስት ራስ ነውና።
23because the husband is head of the wife, as also the Christ [is] head of the assembly, and he is saviour of the body,
24ዳሩ ግን ቤተ ክርስቲያን ለክርስቶስ እንደምትገዛ እንዲሁ ሚስቶች ደግሞ በሁሉ ለባሎቻቸው ይገዙ።
24but even as the assembly is subject to Christ, so also [are] the wives to their own husbands in everything.
25ባሎች ሆይ፥ ክርስቶስ ደግሞ ቤተ ክርስቲያንን እንደ ወደዳት ሚስቶቻችሁን ውደዱ፤ በውኃ መታጠብና ከቃሉ ጋር አንጽቶ እንዲቀድሳት ስለ እርስዋ ራሱን አሳልፎ ሰጠ፤
25The husbands! love your own wives, as also the Christ did love the assembly, and did give himself for it,
27እድፈት ወይም የፊት መጨማደድ ወይም እንዲህ ያለ ነገር ሳይሆንባት ቅድስትና ያለ ነውር ትሆን ዘንድ ክብርት የሆነችን ቤተ ክርስቲያን ለራሱ እንዲያቀርብ ፈለገ።
26that he might sanctify it, having cleansed [it] with the bathing of the water in the saying,
28እንዲሁም ባሎች ደግሞ እንደ ገዛ ሥጋቸው አድርገው የገዛ ሚስቶቻቸውን ሊወዱአቸው ይገባቸዋል። የገዛ ሚስቱን የሚወድ ራሱን ይወዳል፤
27that he might present it to himself the assembly in glory, not having spot or wrinkle, or any of such things, but that it may be holy and unblemished;
29ማንም የገዛ ሥጋውን የሚጠላ ከቶ የለምና፥ ነገር ግን የአካሉ ብልቶች ስለሆንን፥ ክርስቶስ ደግሞ ለቤተ ክርስቲያን እንዳደረገላት፥ ይመግበዋል ይከባከበውማል።
28so ought the husbands to love their own wives as their own bodies: he who is loving his own wife — himself he doth love;
31ስለዚህ ሰው አባቱንና እናቱን ይተዋል ከሚስቱም ጋር ይተባበራል ሁለቱም አንድ ሥጋ ይሆናሉ።
29for no one ever his own flesh did hate, but doth nourish and cherish it, as also the Lord — the assembly,
32ይህ ምሥጢር ታላቅ ነው፥ እኔ ግን ይህን ስለ ክርስቶስና ስለ ቤተ ክርስቲያን እላለሁ።
30because members we are of his body, of his flesh, and of his bones;
33ሆኖም ከእናንተ ደግሞ እያንዳንዱ የገዛ ሚስቱን እንዲህ እንደ ራሱ አድርጎ ይውደዳት፥ ሚስቱም ባልዋን ትፍራ።
31`for this cause shall a man leave his father and mother, and shall be joined to his wife, and they shall be — the two — for one flesh;`
32this secret is great, and I speak in regard to Christ and to the assembly;
33but ye also, every one in particular — let each his own wife so love as himself, and the wife — that she may reverence the husband.