Young`s Literal Translation

Amharic: New Testament

Galatians

1

1Paul, an apostle — not from men, nor through man, but through Jesus Christ, and God the Father, who did raise him out of the dead —
1በኢየሱስ ክርስቶስ ከሙታንም ባነሣው በእግዚአብሔር አብ ሐዋርያ የሆነ እንጂ ከሰዎች ወይም በሰው ያልሆነ ጳውሎስ ከእኔም ጋር ያሉት ወንድሞች ሁሉ፥ ወደ ገላትያ አብያተ ክርስቲያናት፤
2and all the brethren with me, to the assemblies of Galatia:
3ከእግዚአብሔር ከአባታችን ከጌታችንም ከኢየሱስ ክርስቶስ ጸጋና ሰላም ለእናንተ ይሁን።
3Grace to you, and peace from God the Father, and our Lord Jesus Christ,
4ክፉ ከሆነ ከአሁኑ ዓለም ያድነን ዘንድ እንደ አምላካችንና እንደ አባታችን ፈቃድ ስለ ኃጢአታችን ራሱን ሰጠ።
4who did give himself for our sins, that he might deliver us out of the present evil age, according to the will of God even our Father,
5ለአብ ከዘላለም እስከ ዘላለም ክብር ይሁን፤ አሜን።
5to whom [is] the glory to the ages of the ages. Amen.
6በክርስቶስ ጸጋ እናንተን ከጠራችሁ ከእርሱ ወደ ልዩ ወንጌል እንዲህ ፈጥናችሁ እንዴት እንዳለፋችሁ እደነቃለሁ፤
6I wonder that ye are so quickly removed from Him who did call you in the grace of Christ to another good news;
7እርሱ ግን ሌላ ወንጌል አይደለም፤ የሚያናውጡአችሁ የክርስቶስንም ወንጌል ሊያጣምሙ የሚወዱ አንዳንዶች አሉ እንጂ።
7that is not another, except there be certain who are troubling you, and wishing to pervert the good news of the Christ;
8ነገር ግን እኛ ብንሆን ወይም ከሰማይ መልአክ፥ ከሰበክንላችሁ ወንጌል የሚለይ ወንጌልን ቢሰብክላችሁ፥ የተረገመ ይሁን።
8but even if we or a messenger out of heaven may proclaim good news to you different from what we did proclaim to you — anathema let him be!
9አስቀድመን እንዳልን እንዲሁ አሁን ሁለተኛ እላለሁ፥ ከተቀበላችሁት የተለየውን ማንም ቢሰብክላችሁ የተረገመ ይሁን።
9as we have said before, and now say again, If any one to you may proclaim good news different from what ye did receive — anathema let him be!
10ሰውን ወይስ እግዚአብሔርን አሁን እሺ አሰኛለሁን? ወይም ሰውን ደስ ላሰኝ እፈልጋለሁን? አሁን ሰውን ደስ ባሰኝ የክርስቶስ ባሪያ ባልሆንሁም።
10for now men do I persuade, or God? or do I seek to please men? for if yet men I did please — Christ`s servant I should not be.
11ወንድሞች ሆይ፥ በእኔ የተሰበከ ወንጌል እንደ ሰው እንዳይደለ አስታውቃችኋለሁ፤
11And I make known to you, brethren, the good news that were proclaimed by me, that it is not according to man,
12ኢየሱስ ክርስቶስ ገልጦልኛል እንጂ እኔ ከሰው አልተቀበልሁትም አልተማርሁትምም።
12for neither did I from man receive it, nor was I taught [it], but through a revelation of Jesus Christ,
13በአይሁድ ሥርዓት በፊት እንዴት እንደ ኖርሁ ሰምታችኋልና፤ የእግዚአብሔርን ቤተ ክርስቲያን ያለ ልክ አሳድድና አጠፋ ነበር፥
13for ye did hear of my behaviour once in Judaism, that exceedingly I was persecuting the assembly of God, and wasting it,
14ለአባቶችም ወግ ከመጠን ይልቅ እየቀናሁ በወገኔ ዘንድ በዘመኔ ካሉት ብዙዎችን በአይሁድ ሥርዓት እበልጥ ነበር።
14and I was advancing in Judaism above many equals in age in mine own race, being more abundantly zealous of my fathers` deliverances,
15ነገር ግን በእናቴ ማኅፀን ሳለሁ የለየኝ በጸጋውም የጠራኝ እግዚአብሔር በአሕዛብ መካከል ስለ እርሱ ወንጌልን እሰብክ ዘንድ ልጁን በእኔ ሁኔታ ሊገልጥ በወደደ ጊዜ፥ ወዲያው ከሥጋና ከደም ጋር አልተማከርሁም፥
15and when God was well pleased — having separated me from the womb of my mother, and having called [me] through His grace —
17ከእኔም በፊት ሐዋርያት ወደ ነበሩት ወደ ኢየሩሳሌም አልወጣሁም፥ ነገር ግን ወደ ዓረብ አገር ሄድሁ እንደ ገናም ወደ ደማስቆ ተመለስሁ።
16to reveal His Son in me, that I might proclaim him good news among the nations, immediately I conferred not with flesh and blood,
18ከዚህ ወዲያ ከሦስት ዓመት በኋላ ኬፋን ልጠይቅ ወደ ኢየሩሳሌም ወጥቼ ከእርሱ ጋር አሥራ አምስት ቀን ሰነበትሁ፤
17nor did I go up to Jerusalem unto those who were apostles before me, but I went away to Arabia, and again returned to Damascus,
19ነገር ግን ከጌታ ወንድም ከያዕቆብ በቀር ከሐዋርያት ሌላ አላየሁም።
18then, after three years I went up to Jerusalem to enquire about Peter, and remained with him fifteen days,
20ስለምፅፍላችሁም ነገር፥ እነሆ፥ በእግዚአብሔር ፊት ሐሰት አልናገርም።
19and other of the apostles I did not see, except James, the brother of the Lord.
21ከዚያ ወዲያ ወደ ሶርያና ወደ ኪልቅያ አገር መጣሁ።
20And the things that I write to you, lo, before God — I lie not;
22በክርስቶስም ያሉት የይሁዳ ማኅበሮች ፊቴን አያውቁም ነበር፤
21then I came to the regions of Syria and of Cilicia,
23ነገር ግን። ቀድሞ እኛን ያሳድድ የነበረ፥ እርሱ በፊት ያጠፋው የነበረውን ሃይማኖት አሁን ይሰብካል ተብሎ ሲነገር ይሰሙ ነበር፤
22and was unknown by face to the assemblies of Judea, that [are] in Christ,
24ስለ እኔም እግዚአብሔርን ያከብሩ ነበር።
23and only they were hearing, that `he who is persecuting us then, doth now proclaim good news — the faith that then he was wasting;`
24and they were glorifying God in me.