Young`s Literal Translation

Amharic: New Testament

Hebrews

3

1Wherefore, holy brethren, partakers of a heavenly calling, consider the apostle and chief priest of our profession, Christ Jesus,
1ስለዚህ፥ ከሰማያዊው ጥሪ ተካፋዮች የሆናችሁ ቅዱሳን ወንድሞች ሆይ፥ የሃይማኖታችንን ሐዋርያና ሊቀ ካህናት ኢየሱስ ክርስቶስን ተመልከቱ፤
2being stedfast to Him who did appoint him, as also Moses in all his house,
2ሙሴ ደግሞ በቤቱ ሁሉ የታመነ እንደሆነ፥ እርሱ ለሾመው የታመነ ነበረ።
3for of more glory than Moses hath this one been counted worthy, inasmuch as more honour than the house hath he who doth build it,
3ቤትን የሚያዘጋጀው ከቤቱ ይልቅ የሚበልጥ ክብር እንዳለው መጠን፥ እንዲሁ እርሱ ከሙሴ ይልቅ የሚበልጥ ክብር የተገባው ሆኖ ተቆጥሮአልና።
4for every house is builded by some one, and He who the all things did build [is] God,
4እያንዳንዱ ቤት በአንድ ሰው ተዘጋጅቶአልና፥ ሁሉን ያዘጋጀ ግን እግዚአብሔር ነው።
5and Moses indeed [was] stedfast in all his house, as an attendant, for a testimony of those things that were to be spoken,
5ሙሴስ በኋላ ስለሚነገረው ነገር ምስክር ሊሆን በቤቱ ሁሉ እንደ ሎሌ የታመነ ነበረ፥ ክርስቶስ ግን እንደ ልጅ በቤቱ ላይ የታመነ ነው፤
6and Christ, as a Son over his house, whose house are we, if the boldness and the rejoicing of the hope unto the end we hold fast.
6እኛም የምንደፍርበትን የምንመካበትንም ተስፋ እስከ መጨረሻው አጽንተን ብንጠብቅ ቤቱ ነን።
7Wherefore, (as the Holy Spirit saith, `To-day, if His voice ye may hear —
7ስለዚህ መንፈስ ቅዱስ እንደሚል።
8ye may not harden your hearts, as in the provocation, in the day of the temptation in the wilderness,
8ዛሬ ድምፁን ብትሰሙት፥ አባቶቻችሁ እኔን የፈተኑበት የመረመሩበትም አርባ ዓመትም ሥራዬን ያዩበት በምድረ በዳ በፈተና ቀን በማስመረር እንደ ሆነ፥ ልባችሁን እልከኛ አታድርጉ።
9in which tempt Me did your fathers, they did prove Me, and saw My works forty years;
10ስለዚህ ያን ትውልድ ተቆጥቼ። ዘወትር በልባቸው ይስታሉ መንገዴን ግን አላወቁም አልሁ፤
10wherefore I was grieved with that generation, and said, Always do they go astray in heart, and these have not known My ways;
11እንዲሁ። ወደ ዕረፍቴ አይገቡም ብዬ በቍጣዬ ማልሁ።
11so I sware in My anger, If they shall enter into My rest — !`)
12ወንድሞች ሆይ፥ ምናልባት ሕያው እግዚአብሔርን የሚያስክዳችሁ ክፉና የማያምን ልብ ከእናንተ በአንዳችሁ እንዳይኖር ተጠንቀቁ፤
12See, brethren, lest there shall be in any of you an evil heart of unbelief in the falling away from the living God,
13ነገር ግን ከእናንተ ማንም በኃጢአት መታለል እልከኛ እንዳይሆን፥ ዛሬ ተብሎ ሲጠራ ሳለ፥ በእያንዳንዱ ቀን እርስ በርሳችሁ ተመካከሩ፤
13but exhort ye one another every day, while the To-day is called, that none of you may be hardened by the deceitfulness of the sin,
14የመጀመሪያ እምነታችንን እስከ መጨረሻው አጽንተን ብንጠብቅ፥ የክርስቶስ ተካፋዮች ሆነናልና፤
14for partakers we have become of the Christ, if the beginning of the confidence unto the end we may hold fast,
15እየተባለ። ዛሬ ድምጹን ብትሰሙት፥ በማስመረር እንደሆነ ልባችሁን እልከኛ አታድርጉ።
15in its being said, `To-day, if His voice ye may hear, ye may not harden your hearts, as in the provocation,`
16ሰምተው ያስመረሩት እነማን ነበሩ? በሙሴ ተመርተው ከግብጽ የወጡ ሁሉ አይደሉምን?
16for certain having heard did provoke, but not all who did come out of Egypt through Moses;
17አርባ አመትም የተቆጣባቸው እነማን ነበሩ? ሬሳቸው በምድረ በዳ የወደቀ፥ ኃጢአትን ያደረጉት እነርሱ አይደሉምን?
17but with whom was He grieved forty years? was it not with those who did sin, whose carcasses fell in the wilderness?
18ካልታዘዙትም በቀር ወደ እረፍቱ እንዳይገቡ የማለባቸው እነማን ነበሩ?
18and to whom did He swear that they shall not enter into His rest, except to those who did not believe? —
19ባለማመናቸውም ጠንቅ ሊገቡ እንዳልተቻላቸው እናያለን።
19and we see that they were not able to enter in because of unbelief.