Young`s Literal Translation

Amharic: New Testament

Hebrews

5

1For every chief priest — out of men taken — in behalf of men is set in things [pertaining] to God, that he may offer both gifts and sacrifices for sins,
1ሊቀ ካህናት ሁሉ ስለ ኃጢአት መባንና መስዋዕትን ሊያቀርብ ከሰው ተመርጦ ለእግዚአብሔር በሆነው ነገር ሁሉ ስለ ሰው ይሾማልና፤
2able to be gentle to those ignorant and going astray, since himself also is compassed with infirmity;
2እርሱ ራሱም ደግሞ ድካምን ስለሚለብስ፥ ላልተማሩትና ለሚስቱት ሊራራላቸው ይችላል፤
3and because of this infirmity he ought, as for the people, so also for himself to offer for sins;
3በዚህም ምክንያት ስለ ሕዝብ እንደሚያቀርብ እንዲሁ ስለ ራሱ ደግሞ መስዋዕትን ስለ ኃጢአት ሊያቀርብ ይገባዋል።
4and no one to himself doth take the honour, but he who is called by God, as also Aaron:
4እንደ አሮንም በእግዚአብሔር ከተጠራ በቀር ማንም ክብሩን ለራሱ የሚወስድ የለም።
5so also the Christ did not glorify himself to become chief priest, but He who spake unto him: `My Son thou art, I to-day have begotten thee;`
5እንዲሁ ክርስቶስ ደግሞ ሊቀ ካህናት ሊሆን ራሱን አላከበረም ነገር ግን። አንተ ልጄ ነህ እኔ ዛሬ ወልጄሃለሁ ያለው እርሱ ነው፤
6as also in another [place] He saith, `Thou [art] a priest — to the age, according to the order of Melchisedek;`
6እንደዚህም በሌላ ስፍራ ደግሞ። አንተ እንደ መልከ ጼዴቅ ሹመት ለዘላለም ካህን ነህ ይላል።
7who in the days of his flesh both prayers and supplications unto Him who was able to save him from death — with strong crying and tears — having offered up, and having been heard in respect to that which he feared,
7እርሱም በስጋው ወራት ከሞት ሊያድነው ወደሚችል ከብርቱ ጩኸትና ከእንባ ጋር ጸሎትንና ምልጃን አቀረበ፥ እግዚአብሔርንም ስለ መፍራቱ ተሰማለት፤
8through being a Son, did learn by the things which he suffered — the obedience,
8ምንም ልጅ ቢሆን፥ ከተቀበለው መከራ መታዘዝን ተማረ፤
9and having been made perfect, he did become to all those obeying him a cause of salvation age-during,
9ከተፈጸመም በኋላ በእግዚአብሔር እንደ መልከ ጼዴቅ ሹመት ሊቀ ካህናት ተብሎ ስለ ተጠራ፥ ለሚታዘዙለት ሁሉ የዘላለም መዳን ምክንያት ሆነላቸው።
10having been addressed by God a chief priest, according to the order of Melchisedek,
11ስለ እርሱም የምንናገረው ብዙ ነገር አለን፥ ጆሮቻችሁም ስለ ፈዘዙ በቃል ልንተረጕመው ጭንቅ ነው።
11concerning whom we have much discourse and of hard explanation to say, since ye have become dull of hearing,
12ከጊዜው የተነሳ አስተማሪዎች ልትሆኑ ሲገባችሁ፥ አንድ ሰው ስለ እግዚአብሔር ቃላት መጀመሪያ ያለውን የሕፃንነትን ትምህርት እንዲያስተምራችሁ እንደ ገና ያስፈልጋችኋልና፤ የሚያስፈልጋችሁም ወተት ነው እንጂ ጠንካራ ምግብ አይደለም።
12for even owing to be teachers, because of the time, again ye have need that one teach you what [are] the elements of the beginning of the oracles of God, and ye have become having need of milk, and not of strong food,
13ወተት የሚጋት ሁሉ ሕፃን ስለ ሆነ የጽድቅን ቃል አያውቅምና፤
13for every one who is partaking of milk [is] unskilled in the word of righteousness — for he is an infant,
14ጠንካራ ምግብ ግን መልካሙንና ክፉውን ለመለየት በስራቸው የለመደ ልቡና ላላቸው ለፍጹማን ሰዎች ነው።
14and of perfect men is the strong food, who because of the use are having the senses exercised, unto the discernment both of good and of evil.