1Then, therefore, did Pilate take Jesus and scourge [him],
1በዚያን ጊዜም ጲላጦስ ኢየሱስን ይዞ ገረፈው።
2and the soldiers having plaited a crown of thorns, did place [it] on his head, and a purple garment they put around him,
2ወታደሮችም ከእሾህ አክሊል ጐንጕነው በራሱ ላይ አኖሩ ቀይ ልብስም አለበሱት፤
3and said, `Hail! the king of the Jews;` and they were giving him slaps.
3እየቀረቡም። የአይሁድ ንጉሥ ሆይ፥ ሰላም ለአንተ ይሁን ይሉት ነበር፤
4Pilate, therefore, again went forth without, and saith to them, `Lo, I do bring him to you without, that ye may know that in him I find no fault;`
4በጥፊም ይመቱት ነበር። ጲላጦስም ደግሞ ወደ ውጭ ወጥቶ። እነሆ፥ አንዲት በደል ስንኳ እንዳላገኘሁበት ታውቁ ዘንድ እርሱን ወደ ውጭ አወጣላችኋለሁ አላቸው።
5Jesus, therefore, came forth without, bearing the thorny crown and the purple garment; and he saith to them, `Lo, the man!`
5ኢየሱስም የእሾህ አክሊል ደፍቶ ቀይ ልብስም ለብሶ ወደ ውጭ ወጣ።
6When, therefore, the chief priests and the officers did see him, they cried out, saying, `Crucify, crucify;` Pilate saith to them, `Take ye him — ye, and crucify; for I find no fault in him;`
6ጲላጦስም። እነሆ ሰውዬው አላቸው። የካህናት አለቆችና ሎሌዎች ባዩትም ጊዜ። ስቀለው ስቀለው እያሉ ጮኹ። ጲላጦስም። እኔስ አንዲት በደል ስንኳ አላገኘሁበትምና እናንተ ወስዳችሁ ስቀሉት አላቸው።
7the Jews answered him, `We have a law, and according to our law he ought to die, for he made himself Son of God.`
7አይሁድም መልሰው። እኛ ሕግ አለን፥ እንደ ሕጋችንም ሊሞት ይገባዋል፥ ራሱን የእግዚአብሔር ልጅ አድርጎአልና አሉት።
8When, therefore, Pilate heard this word, he was the more afraid,
8ስለዚህ ጲላጦስ ይህን ነገር በሰማ ጊዜ እግጅ ፈራ፤
9and entered again to the praetorium, and saith to Jesus, `Whence art thou?` and Jesus gave him no answer.
9ተመልሶም ወደ ገዡ ግቢ ገባና ኢየሱስን። አንተ ከወዴት ነህ? አለው። ኢየሱስ ግን አንድ እንኳ አልመለሰለትም።
10Pilate, therefore, saith to him, `To me dost thou not speak? hast thou not known that I have authority to crucify thee, and I have authority to release thee?`
10ስለዚህ ጲላጦስ። አትነግረኝምን? ልሰቅልህ ሥልጣን እንዳለኝ ወይም ልፈታህ ሥልጣን እንዳለኝ አታውቅምን? አለው።
11Jesus answered, `Thou wouldst have no authority against me, if it were not having been given thee from above; because of this, he who is delivering me up to thee hath greater sin.`
11ኢየሱስም መልሶ። ከላይ ካልተሰጠህ በቀር በእኔ ላይ ምንም ሥልጣን ባልነበረህም፤ ስለዚህ ለአንተ አሳልፎ የሰጠኝ ኃጢአቱ የባሰ ነው አለው።
12From this [time] was Pilate seeking to release him, and the Jews were crying out, saying, `If this one thou mayest release, thou art not a friend of Caesar; every one making himself a king, doth speak against Caesar.`
12ከዚህ በኋላ ጲላጦስ ሊፈታው ፈለገ፤ ነገር ግን አይሁድ። ይህንስ ብትፈታው የቄሣር ወዳጅ አይደለህም፤ ራሱን ንጉሥ የሚያደርግ ሁሉ የቄሣር ተቃዋሚ ነው እያሉ ጮኹ።
13Pilate, therefore, having heard this word, brought Jesus without — and he sat down upon the tribunal — to a place called, `Pavement,` and in Hebrew, Gabbatha;
13ጲላጦስም ይህን ነገር ሰምቶ ኢየሱስን ወደ ውጭ አወጣው፥ በዕብራይስጥም ገበታ በተባለው ጸፍጸፍ በሚሉት ስፍራ በፍርድ ወንበር ተቀመጠ።
14and it was the preparation of the passover, and as it were the sixth hour, and he saith to the Jews, `Lo, your king!`
14ለፋሲካም የማዘጋጀት ቀን ነበረ፤ ስድስት ሰዓትም የሚያህል ነበረ፤ አይሁድንም። እነሆ ንጉሣችሁ አላቸው።
15and they cried out, `Take away, take away, crucify him;` Pilate saith to them, `Your king shall I crucify?` the chief priests answered, `We have no king except Caesar.`
15እነርሱ ግን። አስወግደው፥ አስወግደው፥ ስቀለው እያሉ ጮኹ። ጲላጦስም። ንጉሣችሁን ልስቀለውን? አላቸው። የካህናት አለቆችም። ከቄሣር በቀር ሌላ ንጉሥ የለንም ብለው መለሱለት።
16Then, therefore, he delivered him up to them, that he may be crucified, and they took Jesus and led [him] away,
16ስለዚህ በዚያን ጊዜ እንዲሰቀል አሳልፎ ሰጣቸው።
17and bearing his cross, he went forth to the place called [Place] of a Skull, which is called in Hebrew Golgotha;
17ኢየሱስንም ይዘው ወሰዱት፤ መስቀሉንም ተሸክሞ በዕብራይስጥ ጎልጎታ ወደ ተባለው የራስ ቅል ስፍራ ወደሚሉት ወጣ።
18where they crucified him, and with him two others, on this side, and on that side, and Jesus in the midst.
18በዚያም ሰቀሉት፥ ከእርሱም ጋር ሌሎች ሁለት፥ አንዱን በዚህ አንዱን በዚያ ኢየሱስንም በመካከላቸው ሰቀሉ።
19And Pilate also wrote a title, and put [it] on the cross, and it was written, `Jesus the Nazarene, the king of the Jews;`
19ጲላጦስም ደግሞ ጽሕፈት ጽፎ በመስቀሉ ላይ አኖረው፤ ጽሕፈቱም። የአይሁድ ንጉሥ የናዝሬቱ ኢየሱስ የሚል ነበረ።
20this title, therefore, read many of the Jews, because the place was nigh to the city where Jesus was crucified, and it was having been written in Hebrew, in Greek, in Roman.
20ኢየሱስም የተሰቀለበት ስፍራ ለከተማ ቅርብ ነበረና ከአይሁድ ብዙዎች ይህን ጽሕፈት አነበቡት፤ በዕብራይስጥና በሮማይስጥ በግሪክም ተጽፎ ነበር።
21The chief priests of the Jews said, therefore, to Pilate, `Write not — The king of the Jews, but that one said, I am king of the Jews;`
21ስለዚህ የአይሁድ ካህናት አለቆች ጲላጦስን። እርሱ። የአይሁድ ንጉስ ነኝ እንዳለ እንጂ የአይሁድ ንጉሥ ብለህ አትጻፍ አሉት።
22Pilate answered, `What I have written, I have written.`
22ጲላጦስም። የጻፍሁትን ጽፌአለሁ ብሎ መለሰ።
23The soldiers, therefore, when they did crucify Jesus, took his garments, and made four parts, to each soldier a part, also the coat, and the coat was seamless, from the top woven throughout,
23ጭፍሮችም ኢየሱስን በሰቀሉት ጊዜ ልብሶቹን ወስደው ለእያንዳንዱ ጭፍራ አንድ ክፍል ሆኖ በአራት ከፋፈሉት፤ እጀጠባቡን ደግሞ ወሰዱ። እጀ ጠባቡም ከላይ ጀምሮ ወጥ ሆኖ የተሠራ ነበረ እንጂ የተሰፋ አልነበረም።
24they said, therefore, to one another, `We may not rend it, but cast a lot for it, whose it shall be;` that the Writing might be fulfilled, that is saying, `They divided my garments to themselves, and upon my raiment they did cast a lot;` the soldiers, therefore, indeed, did these things.
24ስለዚህ እርስ በርሳቸው። ለማን እንዲሆን በእርሱ ዕጣ እንጣጣልበት እንጂ አንቅደደው ተባባሉ። ይህም። ልብሴን እርስ በርሳቸው ተከፋፈሉ በእጀ ጠባቤም ዕጣ ተጣጣሉበት የሚለው የመጽሐፍ ቃል ይፈጸም ዘንድ ነው።
25And there stood by the cross of Jesus his mother, and his mother`s sister, Mary of Cleopas, and Mary the Magdalene;
25ጭፍሮችም እንዲህ አደረጉ። ነገር ግን በኢየሱስ መስቀል አጠገብ እናቱ፥ የእናቱም እኅት፥ የቀለዮጳም ሚስት ማርያም፥ መግደላዊትም ማርያም ቆመው ነበር።
26Jesus, therefore, having seen [his] mother, and the disciple standing by, whom he was loving, he saith to his mother, `Woman, lo, thy son;`
26ኢየሱስም እናቱን ይወደው የነበረውንም ደቀ መዝሙር በአጠገቡ ቆሞ ባየ ጊዜ እናቱን። አንቺ ሴት፥ እነሆ ልጅሽ አላት።
27afterward he saith to the disciple, `Lo, thy mother;` and from that hour the disciple took her to his own [home].
27ከዚህ በኋላ ደቀ መዝሙሩን። እናትህ እነኋት አለው። ከዚህም ሰዓት ጀምሮ ደቀ መዝሙሩ ወደ ቤቱ ወሰዳት።
28After this, Jesus knowing that all things now have been finished, that the Writing may be fulfilled, saith, `I thirst;`
28ከዚህ በኋላ ኢየሱስ አሁን ሁሉ እንደተፈጸመ አውቆ የመጽሐፉ ቃል ይፈጸም ዘንድ። ተጠማሁ አለ።
29a vessel, therefore, was placed full of vinegar, and they having filled a sponge with vinegar, and having put [it] around a hyssop stalk, did put [it] to his mouth;
29በዚያም ሆምጣጤ የሞላበት ዕቃ ተቀምጦ ነበር፤ እነርሱም ሆምጣጤውን በሰፍነግ ሞልተው በሁሶፕም አድርገው ወደ አፉ አቀረቡለት።
30when, therefore, Jesus received the vinegar, he said, `It hath been finished;` and having bowed the head, gave up the spirit.
30ኢየሱስም ሆምጣጤውን ከተቀበለ በኋላ። ተፈጸመ አለ፥ ራሱንም አዘንብሎ ነፍሱን አሳልፎ ሰጠ።
31The Jews, therefore, that the bodies might not remain on the cross on the sabbath, since it was the preparation, (for that sabbath day was a great one,) asked of Pilate that their legs may be broken, and they taken away.
31አይሁድም የማዘጋጀት ቀን ስለ ሆነ ያ ሰንበት ትልቅ ነበረና ሥጋቸው በሰንበት በመስቀል ላይ እንዳይኖር፥ ጭናቸውን ሰብረው እንዲያወርዱአቸው ጲላጦስን ለመኑት።
32The soldiers, therefore, came, and of the first indeed they did break the legs, and of the other who was crucified with him,
32ጭፍሮችም መጥተው የፊተኛውን ጭን ከእርሱም ጋር የተሰቀለውን የሌላውን ጭን ሰበሩ፤
33and having come to Jesus, when they saw him already having been dead, they did not break his legs;
33ወደ ኢየሱስ በመጡ ጊዜ ግን እርሱ ፈጽሞ እንደ ሞተ አይተው ጭኑን አልሰበሩም፤
34but one of the soldiers with a spear did pierce his side, and immediately there came forth blood and water;
34ነገር ግን ከጭፍሮች አንዱ ጎኑን በጦር ወጋው፤ ወዲያውም ደምና ውኃ ወጣ።
35and he who hath seen hath testified, and his testimony is true, and that one hath known that true things he speaketh, that ye also may believe.
35ያየውም መስክሮአል፤ ምስክሩም እውነት ነው፤ እናንተም ደግሞ ታምኑ ዘንድ እርሱ እውነት እንዲናገር ያውቃል።
36For these things came to pass, that the Writing may be fulfilled, `A bone of him shall not be broken;`
36ይህ የሆነ። ከእርሱ አጥንት አይሰበርም የሚል የመጽሐፉ ቃል እንዲፈጸም ነው።
37and again another Writing saith, `They shall look to him whom they did pierce.`
37ደግሞም ሌላው መጽሐፍ። የወጉትን ያዩታል ይላል።
38And after these things did Joseph of Arimathea — being a disciple of Jesus, but concealed, through the fear of the Jews — ask of Pilate, that he may take away the body of Jesus, and Pilate gave leave; he came, therefore, and took away the body of Jesus,
38ከዚህም በኋላ አይሁድን ስለ ፈራ በስውር የኢየሱስ ደቀ መዝሙር የነበረ የአርማትያስ ዮሴፍ የኢየሱስን ሥጋ ሊወስድ ጲላጦስን ለመነ፤ ጲላጦስም ፈቀደለት። ስለዚህም መጥቶ የኢየሱስን ሥጋ ወሰደ።
39and Nicodemus also came — who came unto Jesus by night at the first — bearing a mixture of myrrh and aloes, as it were, a hundred pounds.
39ደግሞም አስቀድሞ በሌሊት ወደ ኢየሱስ መጥቶ የነበረ ኒቆዲሞስ መቶ ንጥር የሚያህል የከርቤና የእሬት ቅልቅል ይዞ መጣ።
40They took, therefore, the body of Jesus, and bound it with linen clothes with the spices, according as it was the custom of the Jews to prepare for burial;
40የኢየሱስንም ሥጋ ወስደው እንደ አይሁድ አገናነዝ ልማድ ከሽቱ ጋር በተልባ እግር ልብስ ከፈኑት።
41and there was in the place where he was crucified a garden, and in the garden a new tomb, in which no one was yet laid;
41በተሰቀለበትም ስፍራ አትክልት ነበረ፥ በአትክልቱም ማንም ገና ያልተቀበረበት አዲስ መቃብር ነበረ።
42there, therefore, because of the preparation of the Jews, because the tomb was nigh, they laid Jesus.
42ስለዚህ መቃብሩ ቅርብ ነበረና ስለ አይሁድ ማዘጋጀት ቀን ኢየሱስን በዚያ አኖሩት።