Young`s Literal Translation

Amharic: New Testament

Luke

1

1Seeing that many did take in hand to set in order a narration of the matters that have been fully assured among us,
1የከበርህ ቴዎፍሎስ ሆይ፥ ከመጀመሪያው በዓይን ያዩትና የቃሉ አገልጋዮች የሆኑት እንዳስተላለፉልን፥ በኛ ዘንድ ስለ ተፈጸመው ነገር ብዙዎች ታሪክን በየተራው ለማዘጋጀት ስለ ሞከሩ፥ እኔ ደግሞ ስለ ተማርኸው ቃል እርግጡን እንድታውቅ በጥንቃቄ ሁሉን ከመጀመሪያው ተከትዬ በየተራው ልጽፍልህ መልካም ሆኖ ታየኝ።
2as they did deliver to us, who from the beginning became eye-witnesses, and officers of the Word, —
5በይሁዳ ንጉሥ በሄሮድስ ዘመን ከአብያ ክፍል የሆነ ዘካርያስ የሚባል አንድ ካህን ነበረ፤ ሚስቱም ከአሮን ልጆች ነበረች፥ ስምዋም ኤልሳቤጥ ነበረ።
3it seemed good also to me, having followed from the first after all things exactly, to write to thee in order, most noble Theophilus,
6ሁለቱም በጌታ ትእዛዝና ሕግጋት ሁሉ ያለ ነቀፋ እየሄዱ በእግዚአብሔር ፊት ጻድቃን ነበሩ።
4that thou mayest know the certainty of the things wherein thou wast instructed.
7ኤልሳቤጥም መካን ነበረችና ልጅ አልነበራቸውም፤ ሁለቱም በዕድሜያቸው አርጅተው ነበር።
5There was in the days of Herod, the king of Judea, a certain priest, by name Zacharias, of the course of Abijah, and his wife of the daughters of Aaron, and her name Elisabeth;
8እርሱም በክፍሉ ተራ በእግዚአብሔር ፊት ሲያገለግል፥
6and they were both righteous before God, going on in all the commands and righteousnesses of the Lord blameless,
9እንደ ካህናት ሥርዓት ወደ ጌታ ቤተ መቅደስ ገብቶ ለማጠን ዕጣ ደረሰበት።
7and they had no child, because that Elisabeth was barren, and both were advanced in their days.
10በዕጣንም ጊዜ ሕዝቡ ሁሉ በውጭ ቆመው ይጸልዩ ነበር።
8And it came to pass, in his acting as priest, in the order of his course before God,
11የጌታም መልአክ በዕጣኑ መሠዊያ ቀኝ ቆሞ ታየው።
9according to the custom of the priesthood, his lot was to make perfume, having gone into the sanctuary of the Lord,
12ዘካርያስም ባየው ጊዜ ደነገጠ፥ ፍርሃትም ወደቀበት።
10and all the multitude of the people were praying without, at the hour of the perfume.
13መልአኩም እንዲህ አለው። ዘካርያስ ሆይ፥ ጸሎትህ ተሰምቶልሃልና አትፍራ ሚስትህ ኤልሳቤጥም ወንድ ልጅ ትወልድልሃለች፥ ስሙንም ዮሐንስ ትለዋለህ።
11And there appeared to him a messenger of the Lord standing on the right side of the altar of the perfume,
14ደስታና ተድላም ይሆንልሃል፥ በመወለዱም ብዙዎች ደስ ይላቸዋል።
12and Zacharias, having seen, was troubled, and fear fell on him;
15በጌታ ፊት ታላቅ ይሆናልና፥ የወይን ጠጅና የሚያሰክር መጠጥ አይጠጣም፤ ገናም በእናቱ ማኅፀን ሳለ መንፈስ ቅዱስ ይሞላበታል፤
13and the messenger said unto him, `Fear not, Zacharias, for thy supplication was heard, and thy wife Elisabeth shall bear a son to thee, and thou shalt call his name John,
16ከእስራኤልም ልጆች ብዙዎችን ወደ ጌታ ወደ አምላካቸው ይመልሳል።
14and there shall be joy to thee, and gladness, and many at his birth shall joy,
17እርሱም የተዘጋጁትን ሕዝብ ለጌታ እንዲያሰናዳ፥ የአባቶችን ልብ ወደ ልጆች የማይታዘዙትንም ወደ ጻድቃን ጥበብ ይመልስ ዘንድ በኤልያስ መንፈስና ኃይል በፊቱ ይሄዳል።
15for he shall be great before the Lord, and wine and strong drink he may not drink, and of the Holy Spirit he shall be full, even from his mother`s womb;
18ዘካርያስም መልአኩን። እኔ ሽማግሌ ነኝ ምስቴም በዕድሜዋ አርጅታለችና ይህን በምን አውቃለሁ? አለው።
16and many of the sons of Israel he shall turn to the Lord their God,
19መልአኩም መልሶ። እኔ በእግዚአብሔር ፊት የምቆመው ገብርኤል ነኝ፥ እንድናገርህም ይህችንም የምሥራች እንድሰብክልህ ተልኬ ነበር፤
17and he shall go before Him, in the spirit and power of Elijah, to turn hearts of fathers unto children, and disobedient ones to the wisdom of righteous ones, to make ready for the Lord, a people prepared.`
20እነሆም፥ በጊዜው የሚፈጸመውን ቃሌን ስላላመንህ፥ ይህ ነገር እስከሚሆን ቀን ድረስ ዲዳ ትሆናለህ መናገርም አትችልም አለው።
18And Zacharias said unto the messenger, `Whereby shall I know this? for I am aged, and my wife is advanced in her days?`
21ሕዝቡም ዘካርያስን ይጠብቁት ነበር፤ በቤተ መቅደስም ውስጥ ስለ ዘገየ ይደነቁ ነበር።
19And the messenger answering said to him, `I am Gabriel, who have been standing near before God, and I was sent to speak unto thee, and to proclaim these good news to thee,
22በወጣም ጊዜ ሊነግራቸው አልቻለም፥ በቤተ መቅደስም ራእይ እንዳየ አስተዋሉ፤ እርሱም ይጠቅሳቸው ነበር፤ ድዳም ሆኖ ኖረ።
20and lo, thou shalt be silent, and not able to speak, till the day that these things shall come to pass, because thou didst not believe my words, that shall be fulfilled in their season.`
23የማገልገሉም ወራት ሲፈጸም ወደ ቤቱ ሄደ።
21And the people were waiting for Zacharias, and wondering at his tarrying in the sanctuary,
24ከዚህም ወራት በኋላ ሚስቱ ኤልሳቤጥ ፀነሰችና። ነቀፌታዬን ከሰው መካከል ያስወግድልኝ ዘንድ ጌታ በተመለከተበት ወራት እንዲህ አድርጎልኛል ስትል ራስዋን አምስት ወር ሰወረች።
22and having come out, he was not able to speak to them, and they perceived that a vision he had seen in the sanctuary, and he was beckoning to them, and did remain dumb.
26በስድስተኛውም ወር መልአኩ ገብርኤል ናዝሬት ወደምትባል ወደ ገሊላ ከተማ፥
23And it came to pass, when the days of his service were fulfilled, he went away to his house,
27ከዳዊት ወገን ለሆነው ዮሴፍ ለሚባል ሰው ወደ ታጨች ወደ አንዲት ድንግል ከእግዚአብሔር ዘንድ ተላከ፥ የድንግሊቱም ስም ማርያም ነበረ።
24and after those days, his wife Elisabeth conceived, and hid herself five months, saying —
28መልአኩም ወደ እርስዋ ገብቶ። ደስ ይበልሽ፥ ጸጋ የሞላብሽ ሆይ፥ ጌታ ከአንቺ ጋር ነው፤ አንቺ ከሴቶች መካከል የተባረክሽ ነሽ አላት።
25`Thus hath the Lord done to me, in days in which He looked upon [me], to take away my reproach among men.`
29እርስዋም ባየችው ጊዜ ከንግግሩ በጣም ደነገጠችና። ይህ እንዴት ያለ ሰላምታ ነው? ብላ አሰበች።
26And in the sixth month was the messenger Gabriel sent by God, to a city of Galilee, the name of which [is] Nazareth,
30መልአኩም እንዲህ አላት። ማርያም ሆይ፥ በእግዚአብሔር ፊት ጸጋ አግኝተሻልና አትፍሪ።
27to a virgin, betrothed to a man, whose name [is] Joseph, of the house of David, and the name of the virgin [is] Mary.
31እነሆም፥ ትፀንሻለሽ ወንድ ልጅም ትወልጃለሽ፥ ስሙንም ኢየሱስ ትዪዋለሽ።
28And the messenger having come in unto her, said, `Hail, favoured one, the Lord [is] with thee; blessed [art] thou among women;`
32እርሱ ታላቅ ይሆናል የልዑል ልጅም ይባላል፥ ጌታ አምላክም የአባቱን የዳዊትን ዙፋን ይሰጠዋል፤
29and she, having seen, was troubled at his word, and was reasoning of what kind this salutation may be.
33በያዕቆብ ቤትም ላይ ለዘለላም ይነግሣል፥ ለመንግሥቱም መጨረሻ የለውም።
30And the messenger said to her, `Fear not, Mary, for thou hast found favour with God;
34ማርያምም መልአኩን። ወንድ ስለማላውቅ ይህ እንዴት ይሆናል? አለችው።
31and lo, thou shalt conceive in the womb, and shalt bring forth a son, and call his name Jesus;
35መልአኩም መልሶ እንዲህ አላት። መንፈስ ቅዱስ በአንቺ ላይ ይመጣል፥ የልዑልም ኃይል ይጸልልሻል ስለዚህ ደግሞ ከአንቺ የሚወለደው ቅዱስ የእግዚአብሔር ልጅ ይባላል።
32he shall be great, and Son of the Highest he shall be called, and the Lord God shall give him the throne of David his father,
36እነሆም ዘመድሽ ኤልሳቤጥ፥ እርስዋ ደግሞ በእርጅናዋ ወንድ ልጅ ፀንሳለች፥ ለእርስዋም መካን ትባል ለነበረችው ይህ ስድስተኛ ወር ነው፤
33and he shall reign over the house of Jacob to the ages; and of his reign there shall be no end.`
37ለእግዚአብሔር የሚሳነው ነገር የለምና።
34And Mary said unto the messenger, `How shall this be, seeing a husband I do not know?`
38ማርያምም። እነሆኝ የጌታ ባሪያ እንደ ቃልህ ይሁንልኝ አለች። መልአኩም ከእርስዋ ሄደ።
35And the messenger answering said to her, `The Holy Spirit shall come upon thee, and the power of the Highest shall overshadow thee, therefore also the holy-begotten thing shall be called Son of God;
39ማርያምም በዚያ ወራት ተነሥታ ወደ ተራራማው አገር ወደ ይሁዳ ከተማ ፈጥና ወጣች፥
36and lo, Elisabeth, thy kinswoman, she also hath conceived a son in her old age, and this is the sixth month to her who was called barren;
40ወደ ዘካርያስም ቤት ገብታ ኤልሳቤጥን ተሳለመቻት።
37because nothing shall be impossible with God.`
41ኤልሳቤጥም የማርያምን ሰላምታ በሰማች ጊዜ ፅንሱ በማኅፀንዋ ውስጥ ዘለለ፤ በኤልሳቤጥም መንፈስ ቅዱስ ሞላባት፥
38And Mary said, `Lo, the maid-servant of the Lord; let it be to me according to thy saying,` and the messenger went away from her.
42በታላቅ ድምፅም ጮኻ እንዲህ አለች። አንቺ ከሴቶች መካከል የተባረክሽ ነሽ፥ የማኅፀንሽም ፍሬ የተባረከ ነው።
39And Mary having arisen in those days, went to the hill-country, with haste, to a city of Judea,
43የጌታዬ እናት ወደ እኔ ትመጣ ዘንድ እንዴት ይሆንልኛል?
40and entered into the house of Zacharias, and saluted Elisabeth.
44እነሆ፥ የሰላምታሽ ድምጽ በጆሮዬ በመጣ ጊዜ ፅንሱ በማኅፀኔ በደስታ ዘሎአልና።
41And it came to pass, when Elisabeth heard the salutation of Mary, the babe did leap in her womb; and Elisabeth was filled with the Holy Spirit,
45ከጌታ፤ የተነገረላት ቃል ይፈጸማልና ያመነች ብፅዕት ናት።
42and spake out with a loud voice, and said, `Blessed [art] thou among women, and blessed [is] the fruit of thy womb;
46ማርያምም እንዲህ አለች።
43and whence [is] this to me, that the mother of my Lord might come unto me?
47ነፍሴ ጌታን ታከብረዋለች፥ መንፈሴም በአምላኬ በመድኃኒቴ ሐሴት ታደርጋለች፤
44for, lo, when the voice of thy salutation came to my ears, leap in gladness did the babe in my womb;
48የባሪያይቱን ውርደት ተመልክቶአልና። እነሆም፥ ከዛሬ ጀምሮ ትውልድ ሁሉ ብፅዕት ይሉኛል፤
45and happy [is] she who did believe, for there shall be a completion to the things spoken to her from the Lord.`
49ብርቱ የሆነ እርሱ በእኔ ታላቅ ሥራ አድርጎአልና፤ ስሙም ቅዱስ ነው።
46And Mary said, `My soul doth magnify the Lord,
50ምሕረቱም ለሚፈሩት እስከ ትውልድና ትውልድ ይኖራል።
47And my spirit was glad on God my Saviour,
51በክንዱ ኃይል አድርጎአል፤ ትዕቢተኞችን በልባቸው አሳብ በትኖአል፤
48Because He looked on the lowliness of His maid-servant, For, lo, henceforth call me happy shall all the generations,
52ገዥዎችን ከዙፋናቸው አዋርዶአል፤ ትሑታንንም ከፍ አድርጎአል፤
49For He who is mighty did to me great things, And holy [is] His name,
53የተራቡትን በበጎ ነገር አጥግቦአል፤ ባለ ጠጎችንም ባዶአቸውን ሰዶአቸዋል።
50And His kindness [is] to generations of generations, To those fearing Him,
54ለአባቶቻችን እንደ ተናገረ፥ ለአብርሃምና ለዘሩ ለዘላለም ምሕረቱ ትዝ እያለው እስራኤልን ብላቴናውን ረድቶአል።
51He did powerfully with His arm, He scattered abroad the proud in the thought of their heart,
56ማርያምም ሦስት ወር የሚያህል በእርስዋ ዘንድ ተቀመጠች ወደ ቤትዋም ተመለሰች።
52He brought down the mighty from thrones, And He exalted the lowly,
57የኤልሳቤጥም የመውለጃዋ ጊዜ ደረሰ፥ ወንድ ልጅም ወለደች።
53The hungry He did fill with good, And the rich He sent away empty,
58ጎረቤቶችዋም ዘመዶችዋም ጌታ ምሕረቱን እንዳገነነላት ሰምተው ከእርስዋ ጋር ደስ አላቸው።
54He received again Israel His servant, To remember kindness,
59በስምንተኛውም ቀን ሕፃኑን ሊገርዙት መጡ፥ በአባቱም ስም ዘካርያስ ሊሉት ወደዱ።
55As He spake unto our fathers, To Abraham and to his seed — to the age.`
60እናቱ ግን መልሳ። አይሆንም፥ ዮሐንስ ይባል እንጂ አለች።
56And Mary remained with her about three months, and turned back to her house.
61እነርሱም። ከወገንሽ ማንም በዚህ ስም የተጠራ የለም አሉአት።
57And to Elisabeth was the time fulfilled for her bringing forth, and she bare a son,
62አባቱንም ማን ሊባል እንዲወድ ጠቀሱት።
58and the neighbours and her kindred heard that the Lord was making His kindness great with her, and they were rejoicing with her.
63ብራናም ለምኖ። ስሙ ዮሐንስ ነው ብሎ ጻፈ። ሁሉም አደነቁ።
59And it came to pass, on the eighth day, they came to circumcise the child, and they were calling him by the name of his father, Zacharias,
64ያንጊዜም አፉ ተከፈተ መላሱም ተፈታ እግዚአብሔርንም እየባረከ ተናገረ።
60and his mother answering said, `No, but he shall be called John.`
65ለጎረቤቶቻቸውም ሁሉ ፍርሃት ሆነ፤ ይህም ሁሉ ነገር በይሁዳ በተራራማው አገር ሁሉ ተወራ፤
61And they said unto her — `There is none among thy kindred who is called by this name,`
66የሰሙትም ሁሉ። እንኪያ ይህ ሕፃን ምን ይሆን? እያሉ በልባቸው አኖሩት፤ የጌታ እጅ ከእርሱ ጋር ነበረችና።
62and they were making signs to his father, what he would wish him to be called,
67አባቱ ዘካርያስም መንፈስ ቅዱስ ሞላበትና ትንቢት ተናገረ እንዲህም አለ።
63and having asked for a tablet, he wrote, saying, `John is his name;` and they did all wonder;
68የእስራኤል ጌታ አምላክ ይባረክ፥ ጐብኝቶ ለሕዝቡ ቤዛ አድርጎአልና፤
64and his mouth was opened presently, and his tongue, and he was speaking, praising God.
69ከጥንት ጀምሮ በነበሩት በቅዱሳን ነቢያት አፍ እንደ ተናገረ፥ በብላቴናው በዳዊት ቤት የመዳን ቀንድን አስነስቶልናል፤
65And fear came upon all those dwelling around them, and in all the hill-country of Judea were all these sayings spoken of,
71ማዳኑም ከወደረኞቻችንና ከሚጠሉን ሁሉ እጅ ነው፤
66and all who heard did lay them up in their hearts, saying, `What then shall this child be?` and the hand of the Lord was with him.
72እንደዚህ ለአባቶቻችን ምሕረት አደረገ፤ ለአባታችን ለአብርሃምም የማለውን መሐላውን ቅዱሱን ኪዳን አሰበ፤
67And Zacharias his father was filled with the Holy Spirit, and did prophesy, saying,
74በእርሱም ከጠላቶቻችን እጅ ድነን በዘመናችን ሁሉ ያለ ፍርሃት በቅድስናና በጽድቅ በፊቱ እንድናገለግለው ሰጠን።
68`Blessed [is] the Lord, the God of Israel, Because He did look upon, And wrought redemption for His people,
76ደግሞም አንተ ሕፃን ሆይ፥ የልዑል ነቢይ ትባላለህ፥ መንገዱን ልትጠርግ በጌታ ፊት ትሄዳለህና፤
69And did raise an horn of salvation to us, In the house of David His servant,
77እንደዚህም የኃጢአታቸው ስርየት የሆነውን የመዳን እውቀት ለሕዝቡ ትሰጣለህ፤
70As He spake by the mouth of His holy prophets, Which have been from the age;
78ይህም ከላይ የመጣ ብርሃን በጐበኘበት በአምላካችን ምሕረትና ርኅራኄ ምክንያት ነው፤
71Salvation from our enemies, And out of the hand of all hating us,
79ብርሃኑም በጨለማና በሞት ጥላ ተቀምጠው ላሉት ያበራል እግሮቻችንንም በሰላም መንገድ ያቀናል።
72To do kindness with our fathers, And to be mindful of His holy covenant,
80ሕፃኑም አደገ በመንፈስም ጠነከረ፥ ለእስራኤልም እስከ ታየበት ቀን ድረስ በምድረ በዳ ኖረ።
73An oath that He sware to Abraham our father,
74To give to us, without fear, Out of the hand of our enemies having been delivered,
75To serve Him, in holiness and righteousness Before Him, all the days of our life.
76And thou, child, Prophet of the Highest Shalt thou be called; For thou shalt go before the face of the Lord, To prepare His ways.
77To give knowledge of salvation to His people In remission of their sins,
78Through the tender mercies of our God, In which the rising from on high did look upon us,
79To give light to those sitting in darkness and death-shade, To guide our feet to a way of peace.`
80And the child grew, and was strengthened in spirit, and he was in the deserts till the day of his shewing unto Israel.