1And he spake also a simile to them, that it behoveth [us] always to pray, and not to faint,
1ሳይታክቱም ዘወትር ሊጸልዩ እንዲገባቸው የሚል ምሳሌን ነገራቸው፥
2saying, `A certain judge was in a certain city — God he is not fearing, and man he is not regarding —
2እንዲህ ሲል። በአንዲት ከተማ እግዚአብሔርን የማይፈራ ሰውንም የማያፍር አንድ ዳኛ ነበረ።
3and a widow was in that city, and she was coming unto him, saying, Do me justice on my opponent,
3በዚያችም ከተማ አንዲት መበለት ነበረች፥ ወደ እርሱም እየመጣች። ከባላጋራዬ ፍረድልኝ ትለው ነበር።
4and he would not for a time, but after these things he said in himself, Even if God I do not fear, and man do not regard,
4አያሌ ቀንም አልወደደም፤ ከዚህ በኋላ ግን በልቡ። ምንም እግዚአብሔርን ባልፈራ ሰውንም ባላፍር፥
5yet because this widow doth give me trouble, I will do her justice, lest, perpetually coming, she may plague me.`
5ይህች መበለት ስለምታደክመኝ ሁልጊዜም እየመጣች እንዳታውከኝ እፈርድላታለሁ አለ።
6And the Lord said, `Hear ye what the unrighteous judge saith:
6ጌታም አለ። ዓመፀኛው ዳኛ ያለውን ስሙ።
7and shall not God execute the justice to His choice ones, who are crying unto Him day and night — bearing long in regard to them?
7እግዚአብሔር እንኪያስ ቀንና ሌሊት ወደ እርሱ ለሚጮኹ ለሚታገሣቸውም ምርጦቹ አይፈርድላቸውምን?
8I say to you, that He will execute the justice to them quickly; but the Son of Man having come, shall he find the faith upon the earth?`
8እላችኋለሁ፥ ፈጥኖ ይፈርድላቸዋል። ነገር ግን የሰው ልጅ በመጣ ጊዜ በምድር እምነትን ያገኝ ይሆንን?
9And he spake also unto certain who have been trusting in themselves that they were righteous, and have been despising the rest, this simile:
9ጻድቃን እንደ ሆኑ በራሳቸው ለሚታመኑና ሌሎቹን ሁሉ በጣም ለሚንቁ ይህን ምሳሌ ነገራቸው፥
10`Two men went up to the temple to pray, the one a Pharisee, and the other a tax-gatherer;
10እንዲህ ሲል። ሁለት ሰዎች ሊጸልዩ ወደ መቅደስ ወጡ፥ አንዱ ፈሪሳዊ ሁለተኛውም ቀራጭ።
11the Pharisee having stood by himself, thus prayed: God, I thank Thee that I am not as the rest of men, rapacious, unrighteous, adulterers, or even as this tax-gatherer;
11ፈሪሳዊም ቆሞ በልቡ ይህን ሲጸልይ። እግዚአብሔር ሆይ፥ እንደ ሌላ ሰው ሁሉ፥ ቀማኞችና ዓመፀኞች አመንዝሮችም፥ ወይም እንደዚህ ቀራጭ ስላልሆንሁ አመሰግንሃለሁ፤
12I fast twice in the week, I give tithes of all things — as many as I possess.
12በየሳምንቱ ሁለት ጊዜ እጦማለሁ፥ ከማገኘውም ሁሉ አሥራት አወጣለሁ አለ።
13`And the tax-gatherer, having stood afar off, would not even the eyes lift up to the heaven, but was smiting on his breast, saying, God be propitious to me — the sinner!
13ቀራጩ ግን በሩቅ ቆሞ ዓይኖቹን ወደ ሰማይ ሊያነሣ እንኳ አልወደደም፥ ነገር ግን። አምላክ ሆይ፥ እኔን ኃጢአተኛውን ማረኝ እያለ ደረቱን ይደቃ ነበር።
14I say to you, this one went down declared righteous, to his house, rather than that one: for every one who is exalting himself shall be humbled, and he who is humbling himself shall be exalted.`
14እላችኋለሁ፥ ከዚያ ይልቅ ይህ ጻድቅ ሆኖ ወደ ቤቱ ተመለሰ፤ ራሱን ከፍ የሚያደርግ ሁሉ ይዋረዳልና፥ ራሱን ግን የሚያዋርድ ከፍ ይላል።
15And they were bringing near also the babes, that he may touch them, and the disciples having seen did rebuke them,
15እንዲዳስሳቸውም ሕፃናትን ደግሞ ወደ እርሱ አመጡ፤ ደቀ መዛሙርቱም አይተው ገሠጹአቸው።
16and Jesus having called them near, said, `Suffer the little children to come unto me, and forbid them not, for of such is the reign of God;
16ኢየሱስ ግን ሕፃናትን ወደ እርሱ ጠርቶ። ሕፃናት ወደ እኔ ይመጡ ዘንድ ተዉአቸው አትከልክሉአቸውም፤ የእግዚአብሔር መንግሥት እንደ እነዚህ ላሉት ናትና።
17verily I say to you, Whoever may not receive the reign of God as a little child, may not enter into it.`
17እውነት እላችኋለሁ፥ የእግዚአብሔርን መንግሥት እንደ ሕፃን የማይቀበላት ሁሉ ከቶ አይገባባትም አለ።
18And a certain ruler questioned him, saying, `Good teacher, what having done — shall I inherit life age-during?`
18ከአለቆችም አንዱ። ቸር መምህር፥ የዘላለምን ሕይወት እንድወርስ ምን ላድርግ? ብሎ ጠየቀው።
19And Jesus said to him, `Why me dost thou call good? no one [is] good, except One — God;
19ኢየሱስም። ስለ ምን ቸር ትለኛለህ? ከአንዱ ከእግዚአብሔር በቀር ቸር ማንም የለም።
20the commands thou hast known: Thou mayest not commit adultery, Thou mayest do no murder, Thou mayest not steal, Thou mayest not bear false witness, Honour thy father and thy mother.`
20ትእዛዛቱን ታውቃለህ፥ አታመንዝር፥ አትግደል፥ አትስረቅ፥ በሐሰት አትመስክር፥ አባትህንና እናትህን አክብር አለው።
21And he said, `All these I did keep from my youth;`
21እርሱም። ይህን ሁሉ ከሕፃንናቴ ጀምሬ ጠብቄአለሁ አለ።
22and having heard these things, Jesus said to him, `Yet one thing to thee is lacking; all things — as many as thou hast — sell, and distribute to the poor, and thou shalt have treasure in heaven, and come, be following me;`
22ኢየሱስም ይህን ሰምቶ። አንዲት ገና ቀርታሃለች፤ ያለህን ሁሉ ሽጠህ ለድሆች ስጥ፥ በሰማይም መዝገብ ታገኛለህ፥ መጥተህም ተከተለኝ አለው።
23and he, having heard these things, became very sorrowful, for he was exceeding rich.
23እርሱ ግን ይህን ሰምቶ እጅግ ባለ ጠጋ ነበርና ብዙ አዘነ።
24And Jesus having seen him become very sorrowful, said, `How hardly shall those having riches enter into the reign of God!
24ኢየሱስም ብዙ እንዳዘነ አይቶ። ገንዘብ ላላቸው ወደ እግዚአብሔር መንግሥት መግባት እንዴት ጭንቅ ይሆናል።
25for it is easier for a camel through the eye of a needle to enter, than for a rich man into the reign of God to enter.`
25ባለ ጠጋ ወደ እግዚአብሔር መንግሥት ከሚገባ ይልቅ ግመል በመርፌ ቀዳዳ ሊገባ ይቀላል አለ።
26And those who heard, said, `And who is able to be saved?`
26የሰሙትም። እንግዲህ ማን ሊድን ይችላል? አሉ።
27and he said, `The things impossible with men are possible with God.`
27እርሱ ግን። በሰው ዘንድ የማይቻል በእግዚአብሔር ዘንድ ይቻላል አለ።
28And Peter said, `Lo, we left all, and did follow thee;`
28ጴጥሮስም። እነሆ፥ እኛ ሁሉን ትተን ተከተልንህ አለ።
29and he said to them, `Verily I say to you, that there is not one who left house, or parents, or brothers, or wife, or children, for the sake of the reign of God,
29እርሱም። እውነት እላችኋለሁ፥ ስለ እግዚአብሔር መንግሥት ቤትን ወይም ወላጆችን ወይም ወንድሞችን ወይም ሚስትን ወይም ልጆችን የተወ፥
30who may not receive back manifold more in this time, and in the coming age, life age-during.`
30በዚህ ዘመን ብዙ እጥፍ በሚመጣውም ዓለም የዘላለምን ሕይወት የማይቀበል ማንም የለም አላቸው።
31And having taken the twelve aside, he said unto them, `Lo, we go up to Jerusalem, and all things shall be completed — that have been written through the prophets — to the Son of Man,
31አሥራ ሁለቱንም ወደ እርሱ አቅርቦ እንዲህ አላቸው። እነሆ፥ ወደ ኢየሩሳሌም እንወጣለን፥ ስለ ሰው ልጅም በነቢያት የተጻፈው ሁሉ ይፈጸማል።
32for he shall be delivered up to the nations, and shall be mocked, and insulted, and spit upon,
32ለአሕዛብ አሳልፈው ይሰጡታልና፥ ይዘብቱበትማል ያንገላቱትማል ይተፉበትማል፤
33and having scourged they shall put him to death, and on the third day he shall rise again.`
33ከገረፉትም በኋላ ይገድሉታል፥ በሦስተኛውም ቀን ይነሣል።
34And they none of these things understood, and this saying was hid from them, and they were not knowing the things said.
34እነርሱም ከዚህ ነገር ምንም አላስተዋሉም፥ ይህም ቃል ተሰውሮባቸው ነበር፥ የተናገረውንም አላወቁም።
35And it came to pass, in his coming nigh to Jericho, a certain blind man was sitting beside the way begging,
35ወደ ኢያሪኮም በቀረበ ጊዜ አንድ ዕውር እየለመነ በመንገድ ዳር ተቀምጦ ነበር።
36and having heard a multitude going by, he was inquiring what this may be,
36ሕዝብም ሲያልፍ ሰምቶ። ይህ ምንድር ነው? ብሎ ጠየቀ።
37and they brought him word that Jesus the Nazarene doth pass by,
37እነርሱም። የናዝሬቱ ኢየሱስ ያልፋል ብለው አወሩለት።
38and he cried out, saying, `Jesus, Son of David, deal kindly with me;`
38እርሱም። የዳዊት ልጅ፥ ኢየሱስ ሆይ፥ ማረኝ እያለ ጮኸ።
39and those going before were rebuking him, that he might be silent, but he was much more crying out, `Son of David, deal kindly with me.`
39በስተ ፊት ይሄዱ የነበሩትም ዝም እንዲል ገሠጹት፤ እርሱ ግን። የዳዊት ልጅ ሆይ፥ ማረኝ እያለ አብዝቶ ጮኸ።
40And Jesus having stood, commanded him to be brought unto him, and he having come nigh, he questioned him,
40ኢየሱስም ቆሞ ወደ እርሱ እንዲያመጡት አዘዘ። በቀረበም ጊዜ። ምን ላደርግልህ ትወዳለህ? ብሎ ጠየቀው።
41saying, `What wilt thou I shall do to thee?` and he said, `Sir, that I may receive sight.`
41እርሱም። ጌታ ሆይ፥ አይ ዘንድ ነው አለው።
42And Jesus said to him, `Receive thy sight; thy faith hath saved thee;`
42ኢየሱስም። እይ፤ እምነትህ አድኖሃል አለው።
43and presently he did receive sight, and was following him, glorifying God; and all the people, having seen, did give praise to God.
43በዚያን ጊዜም አየ፥ እግዚአብሔንም እያከበረ ተከተለው። ሕዝቡም ሁሉ አይተው እግዚአብሔርን አመሰገኑ።