1And having looked up, he saw those who did cast their gifts to the treasury — rich men,
1ዓይኑንም አንሥቶ መባቸውን በመዝገብ የሚጥሉ ባለ ጠጎችን አየ።
2and he saw also a certain poor widow casting there two mites,
2አንዲትም ድሀ መበለት ሁለት ሳንቲም በዚያ ስትጥል አየና።
3and he said, `Truly I say to you, that this poor widow did cast in more than all;
3እውነት እላችኋለሁ፥ ይህች ድሀ መበለት ከሁሉ ይልቅ አብልጣ ጣለች፤
4for all these out of their superabundance did cast into the gifts to God, but this one out of her want, all the living that she had, did cast in.`
4እነዚህ ሁሉ ከትርፋቸው ወደ እግዚአብሔር መዝገብ ጥለዋልና፤ ይህች ግን ከጕድለትዋ የነበራትን ትዳርዋን ሁሉ ጣለች አለ።
5And certain saying about the temple, that with goodly stones and devoted things it hath been adorned, he said,
5አንዳንዶቹም ስለ መቅደስ በመልካም ድንጋይና በተሰጠው ሽልማት እንዳጌጠ ሲነጋገሩ። ይህማ የምታዩት ሁሉ፥
6`These things that ye behold — days will come, in which there shall not be left a stone upon a stone, that shall not be thrown down.`
6ድንጋይ በድንጋይ ላይ ሳይፈርስ በዚህ የማይቀርበት ዘመን ይመጣል አለ።
7And they questioned him, saying, `Teacher, when, then, shall these things be? and what [is] the sign when these things may be about to happen?`
7እነርሱም። መምህር ሆይ፥ እንግዲህ ይህ መቼ ይሆናል? ይህስ ይሆን ዘንድ እንዳለው ምልክቱ ምንድር ነው? ብለው ጠየቁት።
8And he said, `See — ye may not be led astray, for many shall come in my name, saying — I am [he], and the time hath come nigh; go not on then after them;
8እንዲህም አለ። እንዳትስቱ ተጠንቀቁ፤ ብዙዎች። እኔ ነኝ፥ ዘመኑም ቀርቦአል እያሉ በስሜ ይመጣሉና፤ እነርሱን ተከትላችሁ አትሂዱ።
9and when ye may hear of wars and uprisings, be not terrified, for it behoveth these things to happen first, but the end [is] not immediately.`
9ጦርንና ሁከትንም በሰማችሁ ጊዜ አትደንግጡ፤ ይህ አስቀድሞ ይሆን ዘንድ ግድ ነውና፥ ነገር ግን መጨረሻው ወዲያው አይሆንም።
10Then said he to them, `Nation shall rise against nation, and kingdom against kingdom,
10በዚያን ጊዜ እንዲህ አላቸው። ሕዝብ በሕዝብ ላይ፥ መንግሥትም በመንግሥት ላይ ይነሣል፤
11great shakings also in every place, and famines, and pestilences, there shall be; fearful things also, and great signs from heaven there shall be;
11ታላቅም የምድር መናወጥና በልዩ ልዩ ስፍራ ቸነፈር ራብም ይሆናል፤ የሚያስፈራም ነገር ከሰማይም ታላቅ ምልክት ይሆናል።
12and before all these, they shall lay on you their hands, and persecute, delivering up to synagogues and prisons, being brought before kings and governors for my name`s sake;
12ከዚህም ሁሉ በፊት እጃቸውን በላያችሁ ይጭናሉ ያሳድዱአችሁማል፤ ስለ ስሜም ወደ ምኵራብና ወደ ወኅኒ አሳልፈው ይሰጡአችኋል፥ ወደ ነገሥታትና ወደ ገዥዎችም ይወስዱአችኋል፤
13and it shall become to you for a testimony.
13ይህም ለምስክርነት ይሆንላችኋል።
14`Settle, then, to your hearts, not to meditate beforehand to reply,
14ሰለዚህ እንዴት እንድትመልሱ አስቀድማችሁ እንዳታስቡ በልባችሁ አኑሩት፤
15for I will give to you a mouth and wisdom that all your opposers shall not be able to refute or resist.
15ወደረኞቻችሁ ሁሉ ሊቃወሙና ሊከራከሩ የማይችሉትን አፍና ጥበብ እሰጣችኋለሁና።
16`And ye shall be delivered up also by parents, and brothers, and kindred, and friends, and they shall put of you to death;
16ወላጆችም ስንኳ ወንድሞችም ዘመዶችም ወዳጆችም አሳልፈው ይሰጡአችኋል፥ ከእናንተም አንዳንዱን ይገድላሉ፤
17and ye shall be hated by all because of my name —
17በሁሉም ስለ ስሜ የተጠላችሁ ትሆናላችሁ።
18and a hair out of your head shall not perish;
18ከራሳችሁም አንዲት ጠጉር ስንኳ አትጠፋም፤
19in your patience possess ye your souls.
19በመታገሣችሁም ነፍሳችሁን ታገኛላችሁ።
20`And when ye may see Jerusalem surrounded by encampments, then know that come nigh did her desolation;
20ኢየሩሳሌም ግን በጭፍራ ተከባ ስታዩ በዚያን ጊዜ ጥፋትዋ እንደ ቀረበ እወቁ።
21then those in Judea, let them flee to the mountains; and those in her midst, let them depart out; and those in the countries, let them not come in to her;
21የዚያን ጊዜ በይሁዳ ያሉ ወደ ተራራዎች ይሽሹ፥ በመካከልዋም ያሉ ከእርስዋ ፈቀቅ ይበሉ፥ በገጠር ያሉም ወደ እርስዋ አይግቡ፤
22because these are days of vengeance, to fulfil all things that have been written.
22የተጻፈው ሁሉ እንዲፈጸም ይህ የበቀል ጊዜ ነውና።
23`And wo to those with child, and to those giving suck, in those days; for there shall be great distress on the land, and wrath on this people;
23በዚያን ወራት ለእርጕዞችና ለሚያጠቡ ወዮላቸው፤ ታላቅ ችግር በምድር ላይ፥ በዚህም ሕዝብ ላይ ቍጣ ይሆናልና፤
24and they shall fall by the mouth of the sword, and shall be led captive to all the nations, and Jerusalem shall be trodden down by nations, till the times of nations be fulfilled.
24በሰይፍ ስለትም ይወድቃሉ፤ ወደ አሕዛብ ሁሉም ይማረካሉ፤ የአሕዛብም ዘመን እስኪፈጸም ድረስ ኢየሩሳሌም በአሕዛብ የተረገጠች ትሆናለች።
25`And there shall be signs in sun, and moon, and stars, and on the land [is] distress of nations with perplexity, sea and billow roaring;
25በፀሐይና በጨረቃም በከዋክብትም ምልክት ይሆናል፤ በምድር ላይም አሕዛብ ከባሕሩና ከሞገዱም ድምፅ የተነሣ እያመነቱ ይጨነቃሉ፤
26men fainting at heart from fear, and expectation of the things coming on the world, for the powers of the heavens shall be shaken.
26ሰዎችም ከፍርሃትና በዓለም የሚመጣበትን ከመጠበቅ የተነሣ ይደክማሉ፤ የሰማያት ኃይላት ይናወጣሉና።
27`And then they shall see the Son of Man, coming in a cloud, with power and much glory;
27በዚያን ጊዜም የሰው ልጅ በኃይልና በብዙ ክብር በደመና ሲመጣ ያዩታል።
28and these things beginning to happen bend yourselves back, and lift up your heads, because your redemption doth draw nigh.`
28ይህም ሊሆን ሲጀምር ቤዛችሁ ቀርቦአልና አሻቅባችሁ ራሳችሁን አንሡ።
29And he spake a simile to them: `See the fig-tree, and all the trees,
29ምሳሌንም ነገራቸው እንዲህ ሲል። በለስንና ዛፎችን ሁሉ እዩ፤
30when they may now cast forth, having seen, of yourselves ye know that now is the summer nigh;
30ሲያቈጠቍጡ ተመልክታችሁ በጋ አሁን እንደ ቀረበ ራሳችሁ ታውቃላችሁ።
31so also ye, when ye may see these things happening, ye know that near is the reign of God;
31እንዲሁ ደግሞ እናንተ ይህ ሁሉ መሆኑን ስታዩ የእግዚአብሔር መንግሥት እንደ ቀረበች እወቁ።
32verily I say to you — This generation may not pass away till all may have come to pass;
32እውነት እላችኋለሁ፥ ይህ ሁሉ እስኪሆን ድረስ ይህ ትውልድ አያልፍም።
33the heaven and the earth shall pass away, but my words may not pass away.
33ሰማይና ምድር ያልፋሉ ቃሌ ግን አያልፍም።
34`And take heed to yourselves, lest your hearts may be weighed down with surfeiting, and drunkenness, and anxieties of life, and suddenly that day may come on you,
34ነገር ግን ልባችሁ በመጠጥ ብዛትና በስካር ስለ ትዳርም በማሰብ እንዳይከብድ፥ ያ ቀንም በድንገት እንዳይመጣባችሁ ለራሳችሁ ተጠንቀቁ፤
35for as a snare it shall come on all those dwelling on the face of all the land,
35በምድር ሁሉ ላይ በሚቀመጡ ሁሉ እንደ ወጥመድ ይደርስባቸዋልና።
36watch ye, then, in every season, praying that ye may be accounted worthy to escape all these things that are about to come to pass, and to stand before the Son of Man.`
36እንግዲህ ሊመጣ ካለው ከዚህ ሁሉ ለማምለጥ፥ በሰው ልጅም ፊት ለመቆም እንድትችሉ ስትጸልዩ ሁል ጊዜ ትጉ።
37And he was during the days in the temple teaching, and during the nights, going forth, he was lodging at the mount called of Olives;
37ዕለት ዕለትም በመቅደስ ያስተምር ነበር፥ ሌሊት ግን ደብረ ዘይት ወደምትባል ተራራ ወጥቶ ያድር ነበር።
38and all the people were coming early unto him in the temple to hear him.
38ሕዝቡም ሁሉ ይሰሙት ዘንድ ማልደው በመቅደስ ወደ እርሱ ይመጡ ነበር።