Young`s Literal Translation

Amharic: New Testament

Luke

23

1And having risen, the whole multitude of them did lead him to Pilate,
1ሁሉም በሞላው ተነሥተው ወደ ጲላጦስ ወሰዱትና።
2and began to accuse him, saying, `This one we found perverting the nation, and forbidding to give tribute to Caesar, saying himself to be Christ a king.`
2ይህ ሕዝባችንን ሲያጣምም ለቄሣርም ግብር እንዳይሰጥ ሲከለክል ደግሞም። እኔ ክርስቶስ ንጉሥ ነኝ ሲል አገኘነው ብለው ይከሱት ጀመር።
3And Pilate questioned him, saying, `Thou art the king of the Jews?` and he answering him, said, `Thou dost say [it].`
3ጲላጦስም። አንተ የአይሁድ ንጉሥ ነህን? ብሎ ጠየቀው። እርሱም መልሶ። አንተ አልህ አለው።
4And Pilate said unto the chief priests, and the multitude, `I find no fault in this man;`
4ጲላጦስም ለካህናት አለቆችና ለሕዝቡ። በዚህ ሰው አንድ በደል ስንኳ አላገኘሁበትም አለ።
5and they were the more urgent, saying — `He doth stir up the people, teaching throughout the whole of Judea — having begun from Galilee — unto this place.`
5እነርሱ ግን አጽንተው። ከገሊላ ጀምሮ እስከዚህ ድረስ በይሁዳ ሁሉ እያስተማረ ሕዝቡን ያውካል አሉ።
6And Pilate having heard of Galilee, questioned if the man is a Galilean,
6ጲላጦስ ግን። ገሊላ ሲሉ በሰማ ጊዜ። የገሊላ ሰው ነውን? ብሎ ጠየቀ፤
7and having known that he is from the jurisdiction of Herod, he sent him back unto Herod, he being also in Jerusalem in those days.
7ከሄሮድስም ግዛት እንደ ሆነ ባወቀ ጊዜ ወደ ሄሮድስ ሰደደው፤ እርሱ ደግሞ በዚያ ጊዜ በኢየሩሳሌም ነበረና።
8And Herod having seen Jesus did rejoice exceedingly, for he was wishing for a long [time] to see him, because of hearing many things about him, and he was hoping some sign to see done by him,
8ሄሮድስም ኢየሱስን ባየው ጊዜ እጅግ ደስ አለው፤ ስለ እርሱ ስለ ሰማ ከብዙ ጊዜ ጀምሮ ሊያየው ይመኝ ነበርና፥ ምልክትም ሲያደርግ ሊያይ ተስፋ ያደርግ ነበር።
9and was questioning him in many words, and he answered him nothing.
9በብዙ ቃልም ጠየቀው፤ እርሱ ግን አንድ ስንኳ አልመለሰለትም።
10And the chief priests and the scribes stood vehemently accusing him,
10የካህናት አለቆችና ጻፎችም አጽንተው ሲከሱት ቆመው ነበር።
11and Herod with his soldiers having set him at nought, and having mocked, having put around him gorgeous apparel, did send him back to Pilate,
11ሄሮድስም ከሠራዊቱ ጋር ናቀው ዘበተበትም፥ የጌጥ ልብስም አልብሶ ወደ ጲላጦስ መልሶ ሰደደው።
12and both Pilate and Herod became friends on that day with one another, for they were before at enmity between themselves.
12ሄሮድስና ጲላጦስም በዚያን ቀን እርስ በርሳቸው ወዳጆች ሆኑ፥ ቀድሞ በመካከላቸው ጥል ነበረና።
13And Pilate having called together the chief priests, and the rulers, and the people,
13ጲላጦስም፥ የካህናትን አለቆችና መኳንንትን ሕዝቡንም በአንድነት ጠርቶ እንዲህ አላቸው።
14said unto them, `Ye brought to me this man as perverting the people, and lo, I before you having examined, found in this man no fault in those things ye bring forward against him;
14ሕዝቡን ያጣምማል ብላችሁ ይህን ሰው ወደ እኔ አመጣችሁት፤ እነሆም፥ በፊታችሁ መርምሬ ከምትከሱበት ነገር አንድ በደል ስንኳ በዚህ ሰው አላገኘሁበትም።
15no, nor yet Herod, for I sent you back unto him, and lo, nothing worthy of death is having been done by him;
15ሄሮድስም ደግሞ ምንም አላገኘም፤ ወደ እኛ መልሶታልና፤ እነሆም፥ ለሞት የሚያደርሰው ምንም አላደረገም፤
16having chastised, therefore, I will release him,`
16እንግዲያስ ቀጥቼ እፈታዋለሁ። በበዓሉ አንድ ይፈታላቸው ዘንድ ግድ ነበረና።
17for it was necessary for him to release to them one at every feast,
18ሁላቸውም በአንድነት። ይህን አስወግድ፥ በርባንንም ፍታልን እያሉ ጮኹ፤
18and they cried out — the whole multitude — saying, `Away with this one, and release to us Barabbas,`
19እርሱም ሁከትን በከተማ አንሥቶ ሰውን ስለ ገደለ በወኅኒ ታስሮ ነበር።
19who had been, because of a certain sedition made in the city, and murder, cast into prison.
20ጲላጦስም ኢየሱስን ሊፈታ ወድዶ ዳግመኛ ተናገራቸው፤
20Pilate again then — wishing to release Jesus — called to them,
21ነገር ግን እነርሱ። ስቀለው ስቀለው እያሉ ይጮኹ ነበር።
21but they were calling out, saying, `Crucify, crucify him.`
22ሦስተኛም። ምን ነው? ያደረገውስ ክፋት ምንድር ነው? ለሞት የሚያደርሰው በደል አላገኘሁበትም፤ ስለዚህ ቀጥቼ እፈታዋለሁ አላቸው።
22And he a third time said unto them, `Why, what evil did he? no cause of death did I find in him; having chastised him, then, I will release [him].`
23እነርሱ ግን እንዲሰቀል በታላቅ ድምፅ አጽንተው ለመኑት። የእነርሱ ጩኸትና የካህናት አለቆችም ቃል በረታ።
23And they were pressing with loud voices asking him to be crucified, and their voices, and those of the chief priests, were prevailing,
24ጲላጦስም ልመናቸው እንዲሆንላቸው ፈረደበት።
24and Pilate gave judgment for their request being done,
25ያንን የለመኑትንም፥ ስለ ሁከት ሰውንም ስለ መግደል በወኅኒ ታስሮ የነበረውን አስፈታላቸው፥ ኢየሱስን ግን ለፈቃዳቸው አሳልፎ ሰጠው።
25and he released him who because of sedition and murder hath been cast into the prison, whom they were asking, and Jesus he gave up to their will.
26በወሰዱትም ጊዜ ስምዖን የተባለ የቀሬናን ሰው ከገጠር ሲመጣ ይዘው ከኢየሱስ በኋላ መስቀሉን እንዲሸከም ጫኑበት።
26And as they led him away, having taken hold on Simon, a certain Cyrenian, coming from the field, they put on him the cross, to bear [it] behind Jesus.
27ዋይ ዋይ ከሚሉና ሙሾ ከሚያወጡ ሴቶችና ከሕዝቡ እጅግ ብዙዎች ተከተሉት።
27And there was following him a great multitude of the people, and of women, who also were beating themselves and lamenting him,
28ኢየሱስ ግን ወደ እነርሱ ዘወር ብሎ እንዲህ አለ። እናንተ የኢየሩሳሌም ልጆች፥ ለእኔስ አታልቅሱልኝ፤ ዳሩ ግን። መካኖችና ያልወለዱ ማኅፀኖች ያላጠቡ ጡቶችም ብፁዓን ናቸው የሚሉበት ጊዜ እነሆ ይመጣልና ለራሳችሁና ለልጆቻችሁ አልቅሱ።
28and Jesus having turned unto them, said, `Daughters of Jerusalem, weep not for me, but for yourselves weep ye, and for your children;
30በዚያን ጊዜ ተራራዎችን። በላያችን ውደቁ፥ ኮረብቶችንም። ሰውሩን ይሉ ዘንድ ይጀምራሉ፤
29for, lo, days do come, in which they shall say, Happy the barren, and wombs that did not bare, and paps that did not give suck;
31በእርጥብ እንጨት እንዲህ የሚያደርጉ ከሆኑ፥ በደረቀውስ እንዴት ይሆን?
30then they shall begin to say to the mountains, Fall on us, and to the hills, Cover us; —
32ሌሎችንም ሁለት ክፉ አድራጊዎች ደግሞ ከእርሱ ጋር ይገድሉ ዘንድ ወሰዱ።
31for, if in the green tree they do these things — in the dry what may happen?`
33ቀራንዮም ወደሚባል ስፍራ በደረሱ ጊዜ፥ በዚያ እርሱን ክፉ አድራጊዎቹንም አንዱን በቀኝ ሁለተኛውንም በግራ ሰቀሉ።
32And there were also others — two evil-doers — with him, to be put to death;
34ኢየሱስም። አባት ሆይ፥ የሚያደርጉትን አያውቁምና ይቅር በላቸው አለ። ልብሱንም ተካፍለው ዕጣ ተጣጣሉበት።
33and when they came to the place that is called Skull, there they crucified him and the evil-doers, one on the right hand and one on the left.
35ሕዝቡም ቆመው ይመለከቱ ነበር። መኳንንቱም ደግሞ። ሌሎችን አዳነ፤ እርሱ በእግዚአብሔር የተመረጠው ክርስቶስ ከሆነ፥ ራሱን ያድን እያሉ ያፌዙበት ነበር።
34And Jesus said, `Father, forgive them, for they have not known what they do;` and parting his garments they cast a lot.
36ጭፍሮችም ደግሞ ወደ እርሱ ቀርበው ሆምጣጤም አምጥተው።
35And the people were standing, looking on, and the rulers also were sneering with them, saying, `Others he saved, let him save himself, if this be the Christ, the choice one of God.`
37አንተስ የአሁድ ንጉሥ ከሆንህ፥ ራስህን አድን እያሉ ይዘብቱበት ነበር።
36And mocking him also were the soldiers, coming near and offering vinegar to him,
38ይህ የአይሁድ ንጉሥ ነው ተብሎ በግሪክና በሮማይስጥ በዕብራይስጥም ፊደል የተጻፈ ጽሕፈት ደግሞ በእርሱ ላይ ነበረ።
37and saying, `If thou be the king of the Jews, save thyself.`
39ከተሰቀሉት ከክፉ አድራጊዎቹም አንዱ። አንተስ ክርስቶስ አይደለህምን? ራስህንም እኛንም አድን ብሎ ሰደበው።
38And there was also a superscription written over him, in letters of Greek, and Roman, and Hebrew, `This is the King of the Jews.`
40ሁለተኛው ግን መልሶ። አንተ እንደዚህ ባለ ፍርድ ሳለህ እግዚአብሔርን ከቶ አትፈራውምን?
39And one of the evil-doers who were hanged, was speaking evil of him, saying, `If thou be the Christ, save thyself and us.`
41ስለ አደረግነውም የሚገባንን እንቀበላለንና በእኛስ እውነተኛ ፍርድ ነው፤ ይህ ግን ምንም ክፋት አላደረገም ብሎ ገሠጸው።
40And the other answering, was rebuking him, saying, `Dost thou not even fear God, that thou art in the same judgment?
42ኢየሱስንም። ጌታ ሆይ፥ በመንግሥትህ በመጣህ ጊዜ አስበኝ አለው።
41and we indeed righteously, for things worthy of what we did we receive back, but this one did nothing out of place;`
43ኢየሱስም። እውነት እልሃለሁ፥ ዛሬ ከእኔ ጋር በገነት ትሆናለህ አለው።
42and he said to Jesus, `Remember me, lord, when thou mayest come in thy reign;`
44ስድስት ሰዓትም ያህል ነበረ፥ ጨለማም እስከ ዘጠኝ ሰዓት በምድር ሁሉ ላይ ሆነ፥ ፀሐይም ጨለመ፥
43and Jesus said to him, `Verily I say to thee, To-day with me thou shalt be in the paradise.`
45የቤተ መቅደስም መጋረጃ ከመካከሉ ተቀደደ።
44And it was, as it were, the sixth hour, and darkness came over all the land till the ninth hour,
46ኢየሱስም በታላቅ ድምፅ ጮኾ። አባት ሆይ፥ ነፍሴን በእጅህ አደራ እሰጣለሁ አለ። ይህንም ብሎ ነፍሱን ሰጠ።
45and the sun was darkened, and the vail of the sanctuary was rent in the midst,
47የመቶ አለቃውም የሆነውን ነገር ባየ ጊዜ። ይህ ሰው በእውነት ጻድቅ ነበረ ብሎ እግዚአብሔርን አከበረ።
46and having cried with a loud voice, Jesus said, `Father, to Thy hands I commit my spirit;` and these things having said, he breathed forth the spirit.
48ይህንም ለማየት ተከማችተው የነበሩ ሕዝብ ሁሉ፥ የሆነውን ባዩ ጊዜ፥ ደረታቸውን እየደቁ ተመለሱ።
47And the centurion having seen what was done, did glorify God, saying, `Really this man was righteous;`
49የሚያውቁቱ ግን ሁሉ ከገሊላ የተከተሉት ሴቶችም ይህን እያዩ በሩቅ ቆመው ነበር።
48and all the multitudes who were come together to this sight, beholding the things that came to pass, smiting their breasts did turn back;
50እነሆም፥ በጎና ጻድቅ ሰው የሸንጎ አማካሪም የሆነ ዮሴፍ የሚባል ሰው ነበረ፤
49and all his acquaintances stood afar off, and women who did follow him from Galilee, beholding these things.
51ይህም በምክራቸውና በሥራቸው አልተባበረም ነበር፤ አርማትያስም ከምትባል ከአይሁድ ከተማ ሆኖ እርሱ ደግሞ የእግዚአብሔርን መንግሥት ይጠባበቅ ነበር።
50And lo, a man, by name Joseph, being a counsellor, a man good and righteous,
52ይኸውም ወደ ጲላጦስ ቀርቦ የኢየሱስን ሥጋ ለመነው፤
51— he was not consenting to their counsel and deed — from Arimathea, a city of the Jews, who also himself was expecting the reign of God,
53አውርዶም በተልባ እግር ልብስ ከፈነው፥ ማንም ገና ባልተቀበረበት ከዓለትም በተወቀረ መቃብር አኖረው።
52he, having gone near to Pilate, asked the body of Jesus,
54የመዘጋጀት ቀንም ነበረ፤ ሰንበትም ሊጀምር ነበረ።
53and having taken it down, he wrapped it in fine linen, and placed it in a tomb hewn out, where no one was yet laid.
55ከገሊላም ከእርሱ ጋር የመጡት ሴቶች ተከትለው መቃብሩን ሥጋውንም እንዴት እንዳኖሩት አዩ።
54And the day was a preparation, and sabbath was approaching,
56ተመልሰውም ሽቱና ቅባት አዘጋጁ። በሰንበትም እንደ ትእዛዙ ዐረፉ።
55and the women also who have come with him out of Galilee having followed after, beheld the tomb, and how his body was placed,
56and having turned back, they made ready spices and ointments, and on the sabbath, indeed, they rested, according to the command.