Young`s Literal Translation

Amharic: New Testament

Mark

15

1And immediately, in the morning, the chief priests having made a consultation, with the elders, and scribes, and the whole sanhedrim, having bound Jesus, did lead away, and delivered [him] to Pilate;
1ወዲያውም ማለዳ የካህናት አለቆች ከሽማግሌዎችና ከጻፎች ከሸንጎውም ሁሉ ጋር ከተማከሩ በኋላ፥ ኢየሱስን አሳስረው ወሰዱትና ለጲላጦስ አሳልፈው ሰጡት።
2and Pilate questioned him, `Art thou the king of the Jews?` and he answering said to him, `Thou dost say [it].`
2ጲላጦስም። አንተ የአይሁድ ንጉሥ ነህን? ብሎ ጠየቀው። እርሱም። አንተ አልህ ብሎ መለሰለት።
3And the chief priests were accusing him of many things, [but he answered nothing.]
3የካህናት አለቆችም ብዙ ያሳጡት ነበር፤ እርሱ ግን ምንም አልመለሰም።
4And Pilate again questioned him, saying, `Thou dost not answer anything! lo, how many things they do testify against thee!`
4ጲላጦስም ደግሞ። አንዳች አትመልስምን? እነሆ፥ በስንት ነገር ያሳጡሃል ብሎ ጠየቀው።
5and Jesus did no more answer anything, so that Pilate wondered.
5ኢየሱስም ከዚያ በኋላ ጲላጦስ እስኪደነቅ ድረስ ምንም አልመለሰም።
6And at every feast he was releasing to them one prisoner, whomsoever they were asking;
6በዚያም በዓል የለመኑትን አንድ እስረኛ ይፈታላቸው ነበር።
7and there was [one] named Barabbas, bound with those making insurrection with him, who had in the insurrection committed murder.
7በዓመፅም ነፍስ ከገደሉት ከዓመፀኞች ጋር የታሰረ በርባን የተባለ ነበረ።
8And the multitude having cried out, began to ask for themselves as he was always doing to them,
8ሕዝቡም ወጥተው እንደ ልማዱ ያደርግላቸው ዘንድ እየጮኹ ይለምኑት ጀመር።
9and Pilate answered them, saying, `Will ye [that] I shall release to you the king of the Jews?`
9ጲላጦስም። የአይሁድን ንጉሥ እፈታላችሁ ዘንድ ትወዳላችሁን? ብሎ መለሰላቸው፤
10for he knew that because of envy the chief priests had delivered him up;
10የካህናት አለቆች በቅንዓት አሳልፈው እንደ ሰጡት ያውቅ ነበርና።
11and the chief priests did move the multitude, that he might rather release Barabbas to them.
11የካህናት አለቆች ግን በርባንን በእርሱ ፈንታ ይፈታላቸው ዘንድ ሕዝቡን አወኩአቸው።
12And Pilate answering, again said to them, `What, then, will ye [that] I shall do to him whom ye call king of the Jews?`
12ጲላጦስም ዳግመኛ መልሶ። እንግዲህ የአይሁድ ንጉሥ የምትሉትን ምን ላደርገው ትወዳላችሁ? አላቸው።
13and they again cried out, `Crucify him.`
13እነርሱም ዳግመኛ። ስቀለው እያሉ ጮኹ።
14And Pilate said to them, `Why — what evil did he?` and they cried out the more vehemently, `Crucify him;`
14ጲላጦስም። ምን ነው? ያደረገው ክፋት ምንድር ነው? አላቸው። እነርሱ ግን። ስቀለው እያሉ ጩኸት አበዙ።
15and Pilate, wishing to content the multitude, released to them Barabbas, and delivered up Jesus — having scourged [him] — that he might be crucified.
15ጲላጦስም የሕዝቡን ፈቃድ ሊያደርግ ወዶ በርባንን ፈታላቸው፥ ኢየሱስንም ገርፎ እንዲሰቀል አሳልፎ ሰጠ።
16And the soldiers led him away into the hall, which is Praetorium, and call together the whole band,
16ወታደሮችም ፕራይቶሪዮን ወደሚባል ግቢ ውስጥ ወሰዱት፥ ጭፍራውንም ሁሉ በአንድነት ጠሩ።
17and clothe him with purple, and having plaited a crown of thorns, they put [it] on him,
17ቀይ ልብስም አለበሱት፥ የእሾህ አክሊልም ጎንጉነው ደፉበት፤
18and began to salute him, `Hail, King of the Jews.`
18የአይሁድ ንጉሥ ሆይ፥ ሰላም ለአንተ ይሁን እያሉ እጅ ይነሱት ጀመር፤
19And they were smiting him on the head with a reed, and were spitting on him, and having bent the knee, were bowing to him,
19ራሱንም በመቃ መቱት ተፉበትም፥ ተንበርክከውም ሰገዱለት።
20and when they [had] mocked him, they took the purple from off him, and clothed him in his own garments, and they led him forth, that they may crucify him.
20ከተዘባበቱበትም በኋላ ቀዩን ልብስ ገፈፉት፥ ልብሱንም አለበሱት፥ ሊሰቅሉትም ወሰዱት።
21And they impress a certain one passing by — Simon, a Cyrenian, coming from the field, the father of Alexander and Rufus — that he may bear his cross,
21አንድ መንገድ አላፊም የአሌክስንድሮስና የሩፎስ አባት ስምዖን የተባለ የቀሬና ሰው ከገጠር ሲመጣ መስቀሉን ይሸከም ዘንድ አስገደዱት።
22and they bring him to the place Golgotha, which is, being interpreted, `Place of a skull;`
22ትርጓሜውም የራስ ቅል ስፍራ ወደሚሆን ጎልጎታ ወደተባለ ስፍራ ወሰዱት።
23and they were giving him to drink wine mingled with myrrh, and he did not receive.
23ከርቤም የተቀላቀለበትን የወይን ጠጅ እንዲጠጣ ሰጡት፤ እርሱ ግን አልተቀበለም።
24And having crucified him, they were dividing his garments, casting a lot upon them, what each may take;
24ሰቀሉትም፥ ልብሱንም ማን ማን እንዲወስድ ዕጣ ተጣጥለው ተካፈሉ።
25and it was the third hour, and they crucified him;
25በሰቀሉትም ጊዜ ሦስት ሰዓት ነበረ።
26and the inscription of his accusation was written above — `The King of the Jews.`
26የክሱ ጽሕፈትም። የአይሁድ ንጉሥ የሚል ተጽፎ ነበር።
27And with him they crucify two robbers, one on the right hand, and one on his left,
27ከእርሱም ጋር ሁለት ወንበዶች አንዱን በቀኙ አንዱንም በግራው ሰቀሉ።
28and the Writing was fulfilled that is saying, `And with lawless ones he was numbered.`
28መጽሐፍም። ከአመፀኞች ጋር ተቆጠረ ያለው ተፈጸመ።
29And those passing by were speaking evil of him, shaking their heads, and saying, `Ah, the thrower down of the sanctuary, and in three days the builder!
29የሚያልፉትም ራሳቸውን እየነቀነቁ ይሰድቡት ነበርና። ዋ፥ ቤተ መቅደስን የምታፈርስ በሦስት ቀንም የምትሠራ፥
30save thyself, and come down from the cross!`
30ከመስቀል ወርደህ ራስህን አድን አሉ።
31And in like manner also the chief priests, mocking with one another, with the scribes, said, `Others he saved; himself he is not able to save.
31እንዲሁም የካህናት አለቆች ደግሞ ከጻፎች ጋር እርስ በርሳቸው እየተዘባበቱ። ሌሎችን አዳነ፤ ራሱን ሊያድን አይችልም፤
32The Christ! the king of Israel — let him come down now from the cross, that we may see and believe;` and those crucified with him were reproaching him.
32አይተን እናምን ዘንድ የእስራኤል ንጉሥ ክርስቶስ አሁን ከመስቀል ይውረድ አሉ። ከእርሱም ጋር የተሰቀሉት ይነቅፉት ነበር።
33And the sixth hour having come, darkness came over the whole land till the ninth hour,
33ስድስት ሰዓትም በሆነ ጊዜ፥ እስከ ዘጠኝ ሰዓት በምድር ሁሉ ላይ ጨለማ ሆነ።
34and at the ninth hour Jesus cried with a great voice, saying, `Eloi, Eloi, lamma sabachthani?` which is, being interpreted, `My God, my God, why didst Thou forsake me?`
34በዘጠኝ ሰዓትም ኢየሱስ። ኤሎሄ፥ ኤሎሄ፥ ላማ ሰበቅታኒ? ብሎ በታላቅ ድምፅ ጮኸ፤ ትርጓሜውም አምላኬ፥ አምላኬ፥ ለምን ተውኸኝ? ማለት ነው።
35And certain of those standing by, having heard, said, `Lo, Elijah he doth call;`
35በዚያም ከቆሙት ሰዎች ሰምተው። እነሆ፥ ኤልያስን ይጠራል አሉ።
36and one having run, and having filled a spunge with vinegar, having put [it] also on a reed, was giving him to drink, saying, `Let alone, let us see if Elijah doth come to take him down.`
36አንዱም ሮጦ ሆምጣጤ በሰፍነግ ሞላ በመቃም አድርጎ። ተዉ፤ ኤልያስ ሊያወርደው ይመጣ እንደ ሆነ እንይ እያለ አጠጣው።
37And Jesus having uttered a loud cry, yielded the spirit,
37ኢየሱስም በታላቅ ድምፅ ጮኸ ነፍሱንም ሰጠ።
38and the veil of the sanctuary was rent in two, from top to bottom,
38የቤተ መቅደስም መጋረጃ ከላይ እስከ ታች ከሁለት ተቀደደ።
39and the centurion who was standing over-against him, having seen that, having so cried out, he yielded the spirit, said, `Truly this man was Son of God.`
39በዚያም በአንጻሩ የቆመ የመቶ አለቃ እንደዚህ ጮኾ ነፍሱን እንደ ሰጠ ባየ ጊዜ። ይህ ሰው በእውነት የእግዚአብሔር ልጅ ነበረ አለ።
40And there were also women afar off beholding, among whom was also Mary the Magdalene, and Mary of James the less, and of Joses, and Salome,
40ሴቶችም ደግሞ በሩቅ ሆነው ይመለከቱ ነበር፤ ከእነርሱም በገሊላ ሳለ ይከተሉትና ያገለግሉት የነበሩ መግደላዊት ማርያም የታናሹ ያዕቆብና የዮሳም እናት ማርያም ሰሎሜም ነበሩ፥ ከእርሱም ጋር ወደ ኢየሩሳሌም የወጡ ሌሎች ብዙዎች ሴቶች ነበሩ።
41(who also, when he was in Galilee, were following him, and were ministering to him,) and many other women who came up with him to Jerusalem.
42አሁንም በመሸ ጊዜ የሰንበት ዋዜማ የሆነ የማዘጋጀት ቀን ስለ ነበረ፥ የከበረ አማካሪ የሆነ የአርማትያስ ዮሴፍ መጣ፥
42And now evening having come, seeing it was the preparation, that is, the fore-sabbath,
43እርሱም ደግሞ የእግዚአብሔርን መንግሥት ይጠባበቅ ነበር፤ ደፍሮም ወደ ጲላጦስ ገባና የኢየሱስን ሥጋ ለመነው።
43Joseph of Arimathea, an honourable counsellor, who also himself was waiting for the reign of God, came, boldly entered in unto Pilate, and asked the body of Jesus.
44ጲላጦስም አሁኑን እንዴት ሞተ ብሎ ተደነቀ፥ የመቶ አለቃውንም ጠርቶ ከሞተ ቆይቶአልን? ብሎ ጠየቀው፤
44And Pilate wondered if he were already dead, and having called near the centurion, did question him if he were long dead,
45ከመቶ አለቃውም ተረድቶ በድኑን ለዮሴፍ ሰጠው።
45and having known [it] from the centurion, he granted the body to Joseph.
46በፍታም ገዝቶ አውርዶም በበፍታ ከፈነው ከዓለትም በተወቀረ መቃብር አኖረው፥ በመቃብሩ ደጃፍም ድንጋይ አንከባለለ።
46And he, having brought fine linen, and having taken him down, wrapped him in the linen, and laid him in a sepulchre that had been hewn out of a rock, and he rolled a stone unto the door of the sepulchre,
47መግደላዊትም ማርያም የዮሳም እናት ማርያም ወዴት እንዳኖሩት ይመለከቱ ነበር።
47and Mary the Magdalene, and Mary of Joses, were beholding where he is laid.