Young`s Literal Translation

Amharic: New Testament

Matthew

1

1A roll of the birth of Jesus Christ, son of David, son of Abraham.
1የዳዊት ልጅ የአብርሃም ልጅ የኢየሱስ ክርስቶስ ትውልድ መጽሐፍ።
2Abraham begat Isaac, and Isaac begat Jacob, and Jacob begat Judah and his brethren,
2አብርሃም ይስሐቅን ወለደ፤ ይስሐቅም ያዕቆብን ወለደ፤ ያዕቆብም ይሁዳንና ወንድሞቹን ወለደ፤
3and Judah begat Pharez and Zarah of Tamar, and Pharez begat Hezron, and Hezron begat Ram,
3ይሁዳም ከትዕማር ፋሬስንና ዛራን ወለደ፤ ፋሬስም ኤስሮምን ወለደ፤
4and Ram begat Amminadab, and Amminadab begat Nahshon, and Nahshon begat Salmon,
4ኤስሮምም አራምን ወለደ፤ አራምም አሚናዳብን ወለደ፤ አሚናዳብም ነአሶንን ወለደ፤ ነአሶንም ሰልሞንን ወለደ፤
5and Salmon begat Boaz of Rahab, and Boaz begat Obed of Ruth, and Obed begat Jesse,
5ሰልሞንም ከራኬብ ቦኤዝን ወለደ፤ ቦኤዝም ከሩት ኢዮቤድን ወለደ፤ ኢዮቤድም እሴይን ወለደ፤
6and Jesse begat David the king. And David the king begat Solomon, of her [who had been] Uriah`s,
6እሴይም ንጉሥ ዳዊትን ወለደ።
7and Solomon begat Rehoboam, and Rehoboam begat Abijah, and Abijah begat Asa,
7ሰሎሞንም ሮብዓምን ወለደ፤ ሮብዓምም አቢያን ወለደ፤ አቢያም አሣፍን ወለደ፤
8and Asa begat Jehoshaphat, and Jehoshaphat begat Joram, and Joram begat Uzziah,
8አሣፍም ኢዮሣፍጥን ወለደ፤ ኢዮሣፍጥም ኢዮራምን ወለደ፤ ኢዮራምም ዖዝያንን ወለደ፤
9and Uzziah begat Jotham, and Jotham begat Ahaz, and Ahaz begat Hezekiah,
9ዖዝያንም ኢዮአታምን ወለደ፤ ኢዮአታምም አካዝን ወለደ፤
10and Hezekiah begat Manasseh, and Manasseh begat Amon, and Amon begat Josiah,
10አካዝም ሕዝቅያስን ወለደ፤ ሕዝቅያስም ምናሴን ወለደ፤ ምናሴም አሞፅን ወለደ፤
11and Josiah begat Jeconiah and his brethren, at the Babylonian removal.
11አሞፅም ኢዮስያስን ወለደ፤ ኢዮስያስም በባቢሎን ምርኮ ጊዜ ኢኮንያንንና ወንድሞቹን ወለደ።
12And after the Babylonian removal, Jeconiah begat Shealtiel, and Shealtiel begat Zerubbabel,
12ከባቢሎንም ምርኮ በኋላ ኢኮንያን ሰላትያልን ወለደ፤ ሰላትያልም ዘሩባቤልን ወለደ፤
13and Zerubbabel begat Abiud, and Abiud begat Eliakim, and Eliakim begat Azor,
13ዘሩባቤልም አብዩድን ወለደ፤ አብዩድም ኤልያቄምን ወለደ፤ ኤልያቄምም አዛርን ወለደ፤
14and Azor begat Sadok, and Sadok begat Achim, and Achim begat Eliud,
14አዛርም ሳዶቅን ወለደ፤ ሳዶቅም አኪምን ወለደ፤ አኪምም ኤልዩድን ወለደ፤
15and Eliud begat Eleazar, and Eleazar begat Matthan, and Matthan begat Jacob,
15ኤልዩድም አልዓዛርን ወለደ፤ አልዓዛርም ማታንን ወለደ፤ ማታንም ያዕቆብን ወለደ፤
16and Jacob begat Joseph, the husband of Mary, of whom was begotten Jesus, who is named Christ.
16ያዕቆብም ክርስቶስ የተባለውን ኢየሱስን የወለደች የማርያምን እጮኛ ዮሴፍን ወለደ።
17All the generations, therefore, from Abraham unto David [are] fourteen generations, and from David unto the Babylonian removal fourteen generations, and from the Babylonian removal unto the Christ, fourteen generations.
17እንግዲህ ትውልድ ሁሉ ከአብርሃም እስከ ዳዊት አሥራ አራት ትውልድ፥ ከዳዊትም እስከ ባቢሎን ምርኮ አሥራ አራት ትውልድ፥ ከባቢሎንም ምርኮ እስከ ክርስቶስ አሥራ አራት ትውልድ ነው።
18And of Jesus Christ, the birth was thus: For his mother Mary having been betrothed to Joseph, before their coming together she was found to have conceived from the Holy Spirit,
18የኢየሱስ ክርስቶስም ልደት እንዲህ ነበረ። እናቱ ማርያም ለዮሴፍ በታጨች ጊዜ ሳይገናኙ ከመንፈስ ቅዱስ ፀንሳ ተገኘች።
19and Joseph her husband being righteous, and not willing to make her an example, did wish privately to send her away.
19እጮኛዋ ዮሴፍም ጻድቅ ሆኖ ሊገልጣት ስላልወደደ በስውር ሊተዋት አሰበ።
20And on his thinking of these things, lo, a messenger of the Lord in a dream appeared to him, saying, `Joseph, son of David, thou mayest not fear to receive Mary thy wife, for that which in her was begotten [is] of the Holy Spirit,
20እርሱ ግን ይህን ሲያስብ፥ እነሆ የጌታ መልአክ በሕልም ታየው፥ እንዲህም አለ። የዳዊት ልጅ ዮሴፍ ሆይ፥ ከእርስዋ የተፀነሰው ከመንፈስ ቅዱስ ነውና እጮኛህን ማርያምን ለመውሰድ አትፍራ።
21and she shall bring forth a son, and thou shalt call his name Jesus, for he shall save his people from their sins.`
21ልጅም ትወልዳለች፤ እርሱ ሕዝቡን ከኃጢአታቸው ያድናቸዋልና ስሙን ኢየሱስ ትለዋለህ።
22And all this hath come to pass, that it may be fulfilled that was spoken by the Lord through the prophet, saying,
22በነቢይ ከጌታ ዘንድ።
23`Lo, the virgin shall conceive, and she shall bring forth a son, and they shall call his name Emmanuel,` which is, being interpreted `With us [he is] God.`
23እነሆ፥ ድንግል ትፀንሳለች ልጅም ትወልዳለች፥ ስሙንም አማኑኤል ይሉታል የተባለው ይፈጸም ዘንድ ይህ ሁሉ ሆኖአል፥ ትርጓሜውም። እግዚአብሔር ከእኛ ጋር የሚል ነው።
24And Joseph, having risen from the sleep, did as the messenger of the Lord directed him, and received his wife,
24ዮሴፍም ከእንቅልፉ ነቅቶ የጌታ መልአክ እንዳዘዘው አደረገ፤ እጮኛውንም ወሰደ፤
25and did not know her till she brought forth her son — the first-born, and he called his name Jesus.
25የበኩር ልጅዋንም እስክትወልድ ድረስ አላወቃትም፤ ስሙንም ኢየሱስ አለው።