Young`s Literal Translation

Amharic: New Testament

Matthew

17

1And after six days Jesus taketh Peter, and James, and John his brother, and doth bring them up to a high mount by themselves,
1ከስድስት ቀንም በኋላ ኢየሱስ ጴጥሮስንና ያዕቆብን ወንድሙንም ዮሐንስን ይዞ ወደ ረጅም ተራራ ብቻቸውን አወጣቸው።
2and he was transfigured before them, and his face shone as the sun, and his garments did become white as the light,
2በፊታቸውም ተለወጠ፥ ፊቱም እንደ ፀሐይ በራ፥ ልብሱም እንደ ብርሃን ነጭ ሆነ።
3and lo, appear to them did Moses and Elijah, talking together with him.
3እነሆም፥ ሙሴና ኤልያስ ከእርሱ ጋር ሲነጋገሩ ታዩአቸው።
4And Peter answering said to Jesus, `Sir, it is good to us to be here; if thou wilt, we may make here three booths — for thee one, and for Moses one, and one for Elijah.`
4ጴጥሮስም መልሶ ኢየሱስን። ጌታ ሆይ፥ በዚህ መሆን ለእኛ መልካም ነው፤ ብትወድስ፥ በዚህ ሦስት ዳስ አንዱን ለአንተ አንዱንም ለሙሴ አንዱንም ለኤልያስ እንሥራ አለ።
5While he is yet speaking, lo, a bright cloud overshadowed them, and lo, a voice out of the cloud, saying, `This is My Son, — the Beloved, in whom I did delight; hear him.`
5እርሱም ገና ሲናገር፥ እነሆ፥ ብሩህ ደመና ጋረዳቸው፥ እነሆም፥ ከደመናው። በእርሱ ደስ የሚለኝ የምወደው ልጄ ይህ ነው፤ እርሱን ስሙት የሚል ድምፅ መጣ።
6And the disciples having heard, did fall upon their face, and were exceedingly afraid,
6ደቀ መዛሙርቱም ሰምተው በፊታቸው ወደቁ እጅግም ፈርተው ነበር።
7and Jesus having come near, touched them, and said, `Rise, be not afraid,`
7ኢየሱስም ቀርቦ ዳሰሳቸውና። ተነሡ አትፍሩም አላቸው።
8and having lifted up their eyes, they saw no one, except Jesus only.
8ዓይናቸውንም አቅንተው ሲያዩ ከኢየሱስ ብቻ በቀር ማንንም አላዩም።
9And as they are coming down from the mount, Jesus charged them, saying, `Say to no one the vision, till the Son of Man out of the dead may rise.`
9ከተራራውም በወረዱ ጊዜ ኢየሱስ። የሰው ልጅ ከሙታን እስኪነሣ ድረስ ያያችሁትን ለማንም አትንገሩ ብሎ አዘዛቸው።
10And his disciples questioned him, saying, `Why then do the scribes say that Elijah it behoveth to come first?`
10ደቀ መዛሙርቱም። እንግዲህ ጻፎች። ኤልያስ አስቀድሞ ሊመጣ ይገባዋል ስለ ምን ይላሉ? ብለው ጠየቁት።
11And Jesus answering said to them, `Elijah doth indeed come first, and shall restore all things,
11ኢየሱስም መልሶ። ኤልያስማ አስቀድሞ ይመጣል ሁሉንም ያቀናል፤
12and I say to you — Elijah did already come, and they did not know him, but did with him whatever they would, so also the Son of Man is about to suffer by them.`
12ነገር ግን እላችኋለሁ፥ ኤልያስ ከዚህ በፊት መጣ፤ የወደዱትንም ሁሉ አደረጉበት እንጂ አላወቁትም፤ እንዲሁም ደግሞ የሰው ልጅ ከእነርሱ መከራ ይቀበል ዘንድ አለው አላቸው።
13Then understood the disciples that concerning John the Baptist he spake to them.
13በዚያን ጊዜ ደቀ መዛሙርቱ ስለ መጥምቁ ስለ ዮሐንስ እንደ ነገራቸው አስተዋሉ።
14And when they came unto the multitude, there came to him a man, kneeling down to him,
14ወደ ሕዝቡም ሲደርሱ አንድ ሰው ወደ እርሱ ቀረበና ተንበርክኮ። ጌታ ሆይ፥ ልጄን ማርልኝ፥ በጨረቃ እየተነሣበት ክፉኛ ይሣቀያልና፤
15and saying, `Sir, deal kindly with my son, for he is lunatic, and doth suffer miserably, for often he doth fall into the fire, and often into the water,
15ብዙ ጊዜ በእሳት ብዙ ጊዜም በውኃ ይወድቃልና።
16and I brought him near to thy disciples, and they were not able to heal him.`
16ወደ ደቀ መዛሙርትህም አመጣሁት ሊፈውሱትም አቃታቸው አለው።
17And Jesus answering said, `O generation, unstedfast and perverse, till when shall I be with you? till when shall I bear you? bring him to me hither;`
17ኢየሱስም መልሶ። የማታምን ጠማማ ትውልድ ሆይ፥ እስከ መቼ ከእናንተ ጋር እኖራለሁ? እስከ መቼስ እታገሣችኋለሁ? ወደዚህ ወደ እኔ አምጡት አለ።
18and Jesus rebuked him, and the demon went out of him, and the lad was healed from that hour.
18ኢየሱስም ገሠጸው ጋኔኑም ከእርሱ ወጣ፥ ብላቴናውም ከዚያች ሰዓት ጀምሮ ተፈወሰ።
19Then the disciples having come to Jesus by himself, said, `Wherefore were we not able to cast him out?`
19ከዚህ በኋላ ደቀ መዛሙርቱ ብቻቸውን ወደ ኢየሱስ ቀረቡና። እኛ ልናወጣው ያልቻልን ስለ ምን ነው? አሉት።
20And Jesus said to them, `Through your want of faith; for verily I say to you, if ye may have faith as a grain of mustard, ye shall say to this mount, Remove hence to yonder place, and it shall remove, and nothing shall be impossible to you,
20ኢየሱስም። ስለ እምነታችሁ ማነስ ነው፤ እውነት እላችኋለሁ፥ የሰናፍጭ ቅንጣት የሚያህል እምነት ቢኖራችሁ፥ ይህን ተራራ። ከዚህ ወደዚያ እለፍ ብትሉት ያልፋል፤ የሚሳናችሁም ነገር የለም።
21and this kind doth not go forth except in prayer and fasting.`
21ይህ ዓይነት ግን ከጸሎትና ከጦም በቀር አይወጣም አላቸው።
22And while they are living in Galilee, Jesus said to them, `The Son of Man is about to be delivered up to the hands of men,
22በገሊላም ሲመላለሱ ኢየሱስ። የሰው ልጅ በሰዎች እጅ አልፎ ይሰጥ ዘንድ አለው፥ ይገድሉትማል፥
23and they shall kill him, and the third day he shall rise,` and they were exceeding sorry.
23በሦስተኛውም ቀን ይነሣል አላቸው። እጅግም አዘኑ።
24And they having come to Capernaum, those receiving the didrachms came near to Peter, and said, `Your teacher — doth he not pay the didrachms?` He saith, `Yes.`
24ወደ ቅፍርናሆምም በመጡ ጊዜ ግብር የሚቀበሉ ሰዎች ወደ ጴጥሮስ ቀረቡና። መምህራችሁ ሁለቱን ዲናር*ፍ1* አይገብርምን? አሉት።
25And when he came into the house, Jesus anticipated him, saying, `What thinkest thou, Simon? the kings of the earth — from whom do they receive custom or poll-tax? from their sons or from the strangers?`
25አዎን ይገብራል አለ። ወደ ቤትም በገባ ጊዜ ኢየሱስ አስቀድሞ። ስምዖን ሆይ፥ ምን ይመስልሃል? የምድር ነገሥታት ቀረጥና ግብር ከማን ይቀበላሉ? ከልጆቻቸውን ወይስ ከእንግዶች? አለው።
26Peter saith to him, `From the strangers.` Jesus said to him, `Then are the sons free;
26ጴጥሮስም። ከእንግዶች ባለው ጊዜ ኢየሱስ። እንኪያስ ልጆቻቸው ነጻ ናቸው።
27but, that we may not cause them to stumble, having gone to the sea, cast a hook, and the fish that hath come up first take thou up, and having opened its mouth, thou shalt find a stater, that having taken, give to them for me and thee.`
27ነገር ግን እንዳናሰናክላቸው፥ ወደ ባሕር ሂድና መቃጥን ጣል፥ መጀመሪያም የሚወጣውን ዓሣ ውሰድና አፉን ስትከፍት እስታቴር*ፍ2* ታገኛለህ፤ ያን ወስደህ ስለ እኔና ስለ አንተ ስጣቸው አለው።