Young`s Literal Translation

Amharic: New Testament

Matthew

26

1And it came to pass, when Jesus finished all these words, he said to his disciples,
1ኢየሱስም እነዚህን ቃሎች ሁሉ በፈጸመ ጊዜ፥
2`Ye have known that after two days the passover cometh, and the Son of Man is delivered up to be crucified.`
2ለደቀ መዛሙርቱ። ከሁለት ቀን በኋላ ፋሲካ እንዲሆን ታውቃላችሁ፥ የሰው ልጅም ሊሰቀል አልፎ ይሰጣል አለ።
3Then were gathered together the chief priests, and the scribes, and the elders of the people, to the court of the chief priest who was called Caiaphas;
3በዚያን ጊዜ የካህናት አለቆች የሕዝብም ሽማግሎች ቀያፋ በሚባለው በሊቀ ካህናቱ ግቢ ተሰበሰቡ፥
4and they consulted together that they might take Jesus by guile, and kill [him],
4ኢየሱስንም በተንኰል ሊያስይዙት ሊገድሉትም ተማከሩ፤
5and they said, `Not in the feast, that there may not be a tumult among the people.`
5ነገር ግን። በሕዝቡ ዘንድ ሁከት እንዳይነሣ በበዓል አይሁን አሉ።
6And Jesus having been in Bethany, in the house of Simon the leper,
6ኢየሱስም በቢታንያ በለምጻሙ በስምዖን ቤት ሳለ፥
7there came to him a woman having an alabaster box of ointment, very precious, and she poured on his head as he is reclining (at meat).
7አንዲት ሴት ዋጋው እጅግ የበዛ ሽቱ የሞላው የአልባስጥሮስ ብልቃጥ ይዛ ወደ እርሱ ቀረበች በማዕድም ተቀምጦ ሳለ በራሱ ላይ አፈሰሰችው።
8And having seen [it], his disciples were much displeased, saying, `To what purpose [is] this waste?
8ደቀ መዛሙርቱም ይህን አይተው ተቈጡና። ይህ ጥፋት ለምንድር ነው?
9for this ointment could have been sold for much, and given to the poor.`
9ይህ በብዙ ዋጋ ተሽጦ ለድሆች ሊሰጥ ይቻል ነበርና አሉ።
10And Jesus having known, said to them, `Why do ye give trouble to the woman? for a good work she wrought for me;
10ኢየሱስም ይህን አውቆ እንዲህ አላቸው። መልካም ሥራ ሠርታልኛለችና ሴቲቱንስ ስለ ምን ታደክሙአታላችሁ?
11for the poor always ye have with you, and me ye have not always;
11ድሆች ሁልጊዜ ከእናንተ ጋር ይኖራሉና፥ እኔ ግን ሁልጊዜ ከእናንተ ጋር አልኖርም፤
12for she having put this ointment on my body — for my burial she did [it].
12እርስዋ ይህን ሽቱ በሰውነቴ ላይ አፍስሳ ለመቃብሬ አደረገች።
13Verily I say to you, Wherever this good news may be proclaimed in the whole world, what this [one] did shall also be spoken of — for a memorial of her.`
13እውነት እላችኋለሁ፥ ይህ ወንጌል በዓለም ሁሉ በማናቸውም ስፍራ በሚሰበክበት እርስዋ ያደረገችው ደግሞ ለእርስዋ መታሰቢያ እንዲሆን ይነገራል።
14Then one of the twelve, who is called Judas Iscariot, having gone unto the chief priests, said,
14በዚያን ጊዜ የአስቆሮቱ ይሁዳ የሚባለው ከአሥራ ሁለቱ አንዱ ወደ ካህናት አለቆች ሄዶ።
15`What are ye willing to give me, and I will deliver him up to you?` and they weighed out to him thirty silverlings,
15ምን ልትሰጡኝ ትወዳላችሁ እኔም አሳልፌ እሰጣችኋለሁ? እነርሱም ሠላሳ ብር መዘኑለት።
16and from that time he was seeking a convenient season to deliver him up.
16ከዚያችም ሰዓት ጀምሮ አሳልፎ ሊሰጠው ምቹ ጊዜ ይሻ ነበር።
17And on the first [day] of the unleavened food came the disciples near to Jesus, saying to him, `Where wilt thou [that] we may prepare for thee to eat the passover?`
17በቂጣው በዓል በመጀመሪያ ቀን ደቀ መዛሙርቱ ወደ ኢየሱስ ቀርበው። ፋሲካን ትበላ ዘንድ ወዴት ልናሰናዳልህ ትወዳለህ አሉት።
18and he said, `Go away to the city, unto such a one, and say to him, The Teacher saith, My time is nigh; near thee I keep the passover, with my disciples;`
18እርሱም። ወደ ከተማ ከእገሌ ዘንድ ሄዳችሁ። መምህር። ጊዜዬ ቀርቦአል፤ ከደቀ መዛሙርቴ ጋር ከአንተ ዘንድ ፋሲካን አደርጋለሁ ይላል በሉት አለ።
19and the disciples did as Jesus appointed them, and prepared the passover.
19ደቀ መዛሙርቱም ኢየሱስ እንዳዘዛቸው አደረጉ ፋሲካንም አሰናዱ።
20And evening having come, he was reclining (at meat) with the twelve,
20በመሸም ጊዜ ከአሥራ ሁለቱ ደቀ መዛሙርቱ ጋር በማዕድ ተቀመጠ።
21and while they are eating, he said, `Verily I say to you, that one of you shall deliver me up.`
21ሲበሉም። እውነት እላችኋለሁ፥ ከእናንተ አንዱ እኔን አሳልፎ ይሰጣል አለ።
22And being grieved exceedingly, they began to say to him, each of them, `Is it I, Sir?`
22እጅግም አዝነው እያንዳንዱ። ጌታ ሆይ፥ እኔ እሆንን? ይሉት ጀመር።
23And he answering said, `He who did dip with me the hand in the dish, he will deliver me up;
23እርሱም መልሶ። ከእኔ ጋር እጁን በወጭቱ ያጠለቀ፥ እኔን አሳልፎ የሚሰጥ እርሱ ነው።
24the Son of Man doth indeed go, as it hath been written concerning him, but wo to that man through whom the Son of Man is delivered up! good it were for him if that man had not been born.`
24የሰው ልጅስ ስለ እርሱ እንደ ተጻፈ ይሄዳል፥ ነገር ግን የሰው ልጅ አልፎ ለሚሰጥበት ለዚያ ሰው ወዮለት፤ ያ ሰው ባልተወለደ ይሻለው ነበር አለ።
25And Judas — he who delivered him up — answering said, `Is it I, Rabbi?` He saith to him, `Thou hast said.`
25አሳልፎ የሚሰጠው ይሁዳም መልሶ። መምህር ሆይ፥ እኔ እሆንን? አለ፤ አንተ አልህ አለው።
26And while they were eating, Jesus having taken the bread, and having blessed, did brake, and was giving to the disciples, and said, `Take, eat, this is my body;`
26ሲበሉም ኢየሱስ እንጀራን አንሥቶ ባረከ ቈርሶም ለደቀ መዛሙርቱ ሰጠና። እንካችሁ፥ ብሉ ይህ ሥጋዬ ነው አለ።
27and having taken the cup, and having given thanks, he gave to them, saying, `Drink ye of it — all;
27ጽዋንም አንሥቶ አመስግኖም ሰጣቸው እንዲህም አለ። ሁላችሁ ከእርሱ ጠጡ፤
28for this is my blood of the new covenant, that for many is being poured out — to remission of sins;
28ስለ ብዙዎች ለኃጢአት ይቅርታ የሚፈስ የአዲስ ኪዳን ደሜ ይህ ነው።
29and I say to you, that I may not drink henceforth on this produce of the vine, till that day when I may drink it with you new in the reign of my Father.`
29ነገር ግን እላችኋለሁ፥ በአባቴ መንግሥት ከእናንተ ጋር ከዚህ ከወይን ፍሬ አዲሱን እስከምጠጣበት እስከዚያ ቀን ድረስ ከዛሬ ጀምሬ አልጠጣውም።
30And having sung a hymn, they went forth to the mount of the Olives;
30መዝሙርም ከዘመሩ በኋላ ወደ ደብረ ዘይት ወጡ።
31then saith Jesus to them, `All ye shall be stumbled at me this night; for it hath been written, I will smite the shepherd, and the sheep of the flock shall be scattered abroad;
31በዚያን ጊዜ ኢየሱስ። በዚች ሌሊት ሁላችሁ በእኔ ትሰናከላላችሁ፤ እረኛውን እመታለሁ የመንጋውም በጎች ይበተናሉ የሚል ተጽፎአልና፤
32but, after my having risen, I will go before you to Galilee.`
32ከተነሣሁ በኋላ ግን ወደ ገሊላ እቀድማችኋለሁ አላቸው።
33And Peter answering said to him, `Even if all shall be stumbled at thee, I will never be stumbled.`
33ጴጥሮስም መልሶ። ሁሉም በአንተ ቢሰናከሉ እኔ ከቶ አልሰናከልም አለው።
34Jesus said to him, `Verily I say to thee, that, this night, before cock-crowing, thrice thou wilt deny me.`
34ኢየሱስ። እውነት እልሃለሁ፥ በዚች ሌሊት ዶሮ ሳይጮኽ ሦስት ጊዜ ትክደኛለህ አለው።
35Peter saith to him, `Even if it may be necessary for me to die with thee, I will not deny thee;` in like manner also said all the disciples.
35ጴጥሮስ። ከአንተ ጋር መሞት እንኳ የሚያስፈልገኝ ቢሆን፥ ከቶ አልክድህም አለው። ደቀ መዛሙርቱ ሁሉ ደግሞ እንደዚሁ አሉ።
36Then come with them doth Jesus to a place called Gethsemane, and he saith to the disciples, `Sit ye here, till having gone away, I shall pray yonder.`
36በዚያን ጊዜ ኢየሱስ ከእነርሱ ጋር ጌቴሴማኒ ወደምትባል ስፍራ መጣ ደቀ መዛሙርቱንም። ወዲያ ሄጄ ስጸልይ ሳለ በዚህ ተቀመጡ አላቸው።
37And having taken Peter, and the two sons of Zebedee, he began to be sorrowful, and to be very heavy;
37ጴጥሮስንም ሁለቱንም የዘብዴዎስን ልጆች ወስዶ ሊያዝን ሊተክዝም ጀመር።
38then saith he to them, `Exceedingly sorrowful is my soul — unto death; abide ye here, and watch with me.`
38ነፍሴ እስከ ሞት ድረስ እጅግ አዘነች፤ በዚህ ቆዩ ከእኔም ጋር ትጉ አላቸው።
39And having gone forward a little, he fell on his face, praying, and saying, `My Father, if it be possible, let this cup pass from me; nevertheless, not as I will, but as Thou.`
39ጥቂትም ወደ ፊት እልፍ ብሎ በፊቱ ወደቀና ሲጸልይ። አባቴ፥ ቢቻልስ፥ ይህች ጽዋ ከእኔ ትለፍ፤ ነገር ግን አንተ እንደምትወድ ይሁን እንጂ እኔ እንደምወድ አይሁን አለ።
40And he cometh unto the disciples, and findeth them sleeping, and he saith to Peter, `So! ye were not able one hour to watch with me!
40ወደ ደቀ መዛሙርቱም መጣ፤ ተኝተውም አገኛቸውና ጴጥሮስን። እንዲሁም ከእኔ ጋር አንዲት ሰዓት እንኳ ልትተጉ አልቻላችሁምን?
41watch, and pray, that ye may not enter into temptation: the spirit indeed is forward, but the flesh weak.`
41ወደ ፈተና እንዳትገቡ ትጉና ጸልዩ፤ መንፈስስ ተዘጋጅታለች ሥጋ ግን ደካማ ነው አለው።
42Again, a second time, having gone away, he prayed, saying, `My Father, if this cup cannot pass away from me except I drink it, Thy will be done;`
42ደግሞ ሁለተኛ ሄዶ ጸለየና። አባቴ፥ ይህች ጽዋ ሳልጠጣት ታልፍ ዘንድ የማይቻል እንደ ሆነ፥ ፈቃድህ ትሁን አለ።
43and having come, he findeth them again sleeping, for their eyes were heavy.
43ደግሞም መጥቶ ዓይኖቻቸው በእንቅልፍ ከብደው ነበርና ተኝተው አገኛቸው።
44And having left them, having gone away again, he prayed a third time, saying the same word;
44ደግሞም ትቶአቸው ሄደ፥ ሦስተኛም ያንኑ ቃል ደግሞ ጸለየ።
45then cometh he unto his disciples, and saith to them, `Sleep on henceforth, and rest! lo, the hour hath come nigh, and the Son of Man is delivered up to the hands of sinners.
45ከዚያ ወዲያ ወደ ደቀ መዛሙርቱ መጥቶ። እንግዲህስ ተኙ ዕረፉም፤ እነሆ፥ ሰዓቲቱ ቀርባለች የሰው ልጅም በኃጢአተኞች እጅ አልፎ ይሰጣል።
46Rise, let us go; lo, he hath come nigh who is delivering me up.`
46ተነሡ፥ እንሂድ፤ እነሆ፥ አሳልፎ የሚሰጠኝ ቀርቦአል አላቸው።
47And while he is yet speaking, lo, Judas, one of the twelve did come, and with him a great multitude, with swords and sticks, from the chief priests and elders of the people.
47ይህንም ገና ሲናገር፥ እነሆ፥ ከአሥራ ሁለቱ አንዱ ይሁዳ መጣ፥ ከእርሱም ጋር ብዙ ሕዝብ ሰይፍና ጐመድ ይዘው ከካህናት አለቆችና ከሕዝቡ ሽማግሎች ዘንድ መጡ።
48And he who did deliver him up did give them a sign, saying, `Whomsoever I will kiss, it is he: lay hold on him;`
48አሳልፎ የሚሰጠውም። የምስመው እርሱ ነው፤ ያዙት ብሎ ምልክት ሰጥቶአቸው ነበር።
49and immediately, having come to Jesus, he said, `Hail, Rabbi,` and kissed him;
49ወዲያውም ወደ ኢየሱስ ቀረበና። መምህር ሆይ፥ ሰላም ለአንተ ይሁን ብሎ ሳመው።
50and Jesus said to him, `Comrade, for what art thou present?` Then having come near, they laid hands on Jesus, and took hold on him.
50ኢየሱስም። ወዳጄ ሆይ፥ ለምን ነገር መጣህ? አለው። በዚያን ጊዜ ቀረቡ እጃቸውንም በኢየሱስ ላይ ጭነው ያዙት።
51And lo, one of those with Jesus, having stretched forth the hand, drew his sword, and having struck the servant of the chief priest, he took off his ear.
51እነሆም፥ ከኢየሱስ ጋር ከነበሩት አንዱ እጁን ዘርግቶ ሰይፉን መዘዘና የሊቀ ካህናቱን ባሪያ መትቶ ጆሮውን ቈረጠው።
52Then saith Jesus to him, `Turn back thy sword to its place; for all who did take the sword, by the sword shall perish;
52በዚያን ጊዜ ኢየሱስ እንዲህ አለው። ሰይፍ የሚያነሡ ሁሉ በሰይፍ ይጠፋሉና ሰይፍህን ወደ ስፍራው መልስ።
53dost thou think that I am not able now to call upon my Father, and He will place beside me more than twelve legions of messengers?
53ወይስ አባቴን እንድለምን እርሱም አሁን ከአሥራ ሁለት ጭፍሮች የሚበዙ መላእክት እንዲሰድልኝ የማይቻል ይመስልሃልን?
54how then may the Writings be fulfilled, that thus it behoveth to happen?`
54እንዲህ ከሆነስ። እንደዚህ ሊሆን ይገባል የሚሉ መጻሕፍት እንዴት ይፈጸማሉ?
55In that hour said Jesus to the multitudes, `As against a robber ye did come forth, with swords and sticks, to take me! daily with you I was sitting teaching in the temple, and ye did not lay hold on me;
55በዚያን ሰዓት ኢየሱስ ለሕዝቡ። ወንበዴን እንደምትይዙ ሰይፍና ጐመድ ይዛችሁ ልትይዙኝ ወጣችሁን? በመቅደስ ዕለት ዕለት እያስተማርሁ ከእናንተ ጋር ስቀመጥ ሳለሁ አልያዛችሁኝም።
56but all this hath come to pass, that the Writings of the prophets may be fulfilled;` then all the disciples, having left him, fled.
56ነገር ግን ይህ ሁሉ የሆነ የነቢያት መጻሕፍት ይፈጸሙ ዘንድ ነው አለ። በዚያን ጊዜ ደቀ መዛሙርቱ ሁሉ ትተውት ሸሹ።
57And those laying hold on Jesus led [him] away unto Caiaphas the chief priest, where the scribes and the elders were gathered together,
57ኢየሱስን የያዙትም ጻፎችና ሽማግሎች ወደ ተከማቹበት ወደ ሊቀ ካህናቱ ወደ ቀያፋ ወሰዱት።
58and Peter was following him afar off, unto the court of the chief priest, and having gone in within, he was sitting with the officers, to see the end.
58ጴጥሮስ ግን እስከ ሊቀ ካህናቱ ግቢ ድረስ ሩቅ ሆኖ ተከተለው፥ የነገሩንም ፍጻሜ ያይ ዘንድ ወደ ውስጥ ገብቶ ከሎሌዎቹ ጋር ተቀመጠ።
59And the chief priests, and the elders, and all the council, were seeking false witness against Jesus, that they might put him to death,
59የካህናት አለቆችና ሽማግሎች ሸንጐውም ሁሉ እንዲገድሉት በኢየሱስ ላይ የሐሰት ምስክር ይፈልጉ ነበር፥ አላገኙም፤
60and they did not find; and many false witnesses having come near, they did not find; and at last two false witnesses having come near,
60ብዙም የሐሰት ምስክሮች ምንም ቢቀርቡ አላገኙም።
61said, `This one said, I am able to throw down the sanctuary of God, and after three days to build it.`
61በኋላም ሁለት ቀርበው። ይህ ሰው። የእግዚአብሔርን ቤተ መቅደስ አፍርሼ በሦስት ቀን ልሠራው እችላለሁ ብሎአል አሉ።
62And the chief priest having stood up, said to him, `Nothing thou dost answer! what do these witness against thee?
62ሊቀ ካህናቱም ተነሥቶ። እነዚህ ለሚመሰክሩብህ አንድ ስንኳ አትመልስምን? አለው።
63and Jesus was silent. And the chief priest answering said to him, `I adjure thee, by the living God, that thou mayest say to us, if thou art the Christ — the Son of God.`
63ኢየሱስ ግን ዝም አለ። ሊቀ ካህናቱም። አንተ የእግዚአብሔር ልጅ ክርስቶስ የሆንህ እንደ ሆነ እንድትነግረን በሕያው እግዚአብሔር አምልሃለሁ አለው።
64Jesus saith to him, `Thou hast said; nevertheless I say to you, hereafter ye shall see the Son of Man sitting on the right hand of the power, and coming upon the clouds, of the heaven.`
64ኢየሱስም። አንተ አልህ ነገር ግን እላችኋለሁ፥ ከእንግዲህ ወዲህ የሰው ልጅ በኃይል ቀኝ ሲቀመጥ በሰማይም ደመና ሲመጣ ታያላችሁ አለው።
65Then the chief priest rent his garments, saying, — `He hath spoken evil; what need have we yet of witnesses? lo, now ye heard his evil speaking;
65በዚያን ጊዜ ሊቀ ካህናቱ ልብሱን ቀዶ። ተሳድቦአል እንግዲህ ወዲህ ምስክሮች ስለ ምን ያስፈልገናል? እነሆ፥ ስድቡን አሁን ሰምታችኋል፤ ምን ይመስላችኋል? አለ።
66what think ye?` and they answering said, `He is worthy of death.`
66እነርሱም። ሞት ይገባዋል ብለው መለሱ።
67Then did they spit in his face and buffet him, and others did slap,
67በዚያን ጊዜ በፊቱ ተፉበት፤ ጐሰሙትም፥ ሌሎችም በጥፊ መትተው። ክርስቶስ ሆይ፥ በጥፊ የመታህ ማን ነው?
68saying, `Declare to us, O Christ, who he is that struck thee?`
68ትንቢት ተናገርልን አሉ።
69And Peter without was sitting in the court, and there came near to him a certain maid, saying, `And thou wast with Jesus of Galilee!`
69ጴጥሮስም ከቤት ውጭ በአጥሩ ግቢ ተቀምጦ ነበር፤ አንዲት ገረድም ወደ እርሱ ቀርባ። አንተ ደግሞ ከገሊላው ከኢየሱስ ጋር ነበርህ አለችው።
70And he denied before all, saying, `I have not known what thou sayest.`
70እርሱ ግን። የምትዪውን አላውቀውም ብሎ በሁሉ ፊት ካደ።
71And he having gone forth to the porch, another female saw him, and saith to those there, `And this one was with Jesus of Nazareth;`
71ወደ በሩም ሲወጣ ሌላይቱ አየችውና በዚያ ላሉት። ይህ ደግሞ ከናዝሬቱ ከኢየሱስ ጋር ነበረ አለች።
72and again did he deny with an oath — `I have not known the man.`
72ዳግመኛም ሲምል። ሰውየውን አላውቀውም ብሎ ካደ።
73And after a little those standing near having come, said to Peter, `Truly thou also art of them, for even thy speech doth make thee manifest.`
73ጥቂትም ቈይተው በዚያ ቆመው የነበሩ ቀርበው ጴጥሮስን። አነጋገርህ ይገልጥሃልና በእውነት አንተ ደግሞ ከእነርሱ ወገን ነህ አሉት።
74Then began he to anathematise, and to swear — `I have not known the man;` and immediately did a cock crow,
74በዚያን ጊዜ። ሰውየውን አላውቀውም ብሎ ሊራገምና ሊምል ጀመረ። ወዲያውም ዶሮ ጮኸ።
75and Peter remembered the saying of Jesus, he having said to him — `Before cock-crowing, thrice thou wilt deny me;` and having gone without, he did weep bitterly.
75ጴጥሮስም። ዶሮ ሳይጮኽ ሦስት ጊዜ ትክደኛለህ ያለው የኢየሱስ ቃል ትዝ አለው፤ ወደ ውጭም ወጥቶ መራራ ልቅሶ አለቀሰ።