1And I saw upon the right hand of Him who is sitting upon the throne a scroll, written within and on the back, sealed with seven seals;
1በዙፋኑ ላይም በተቀመጠው በቀኝ እጁ ላይ በውስጥና በኋላ የተጻፈበት በሰባትም ማኅተም የተዘጋ መጽሐፍን አየሁ።
2and I saw a strong messenger crying with a great voice, `Who is worthy to open the scroll and to loose the seals of it?`
2ብርቱም መልአክ። መጽሐፉን ይዘረጋ ዘንድ ማኅተሞቹንም ይፈታ ዘንድ የሚገባው ማን ነው? ብሎ በታላቅ ድምፅ ሲያውጅ አየሁ።
3and no one was able in the heaven, nor upon the earth, nor under the earth, to open the scroll, nor to behold it.
3በሰማይም ቢሆን በምድርም ላይ ቢሆን ከምድርም በታች ቢሆን መጽሐፉን ሊዘረጋ ወይም ሊመለከተው ማንም አልተቻለውም።
4And I was weeping much, because no one was found worthy to open and to read the scroll, nor to behold it,
4መጽሐፉን ሊዘረጋ ወይም ሊመለከተው የሚገባው ማንም ስላልተገኘ እጅግ አለቀስሁ።
5and one of the elders saith to me, `Weep not; lo, overcome did the Lion, who is of the tribe of Judah, the root of David, to open the scroll, and to loose the seven seals of it;
5ከሽማግሌዎቹም አንዱ። አታልቅስ፤ እነሆ፥ ከይሁዳ ነገድ የሆነው አንበሳ እርሱም የዳዊት ሥር መጽሐፉን ይዘረጋ ዘንድ ሰባቱንም ማኅተም ይፈታ ዘንድ ድል ነሥቶአል አለኝ።
6and I saw, and lo, in the midst of the throne, and of the four living creatures, and in the midst of the elders, a Lamb hath stood as it had been slain, having seven horns and seven eyes, which are the Seven Spirits of God, which are sent to all the earth,
6በዙፋኑና በአራቱ እንስሶች መካከልም በሽማግሌዎችም መካከል እንደ ታረደ በግ ቆሞ አየሁ፥ ሰባትም ቀንዶችና ሰባት ዓይኖች ነበሩት እነርሱም ወደ ምድር ሁሉ የተላኩ የእግዚአብሔር መናፍስት ናቸው።
7and he came and took the scroll out of the right hand of Him who is sitting upon the throne.
7መጥቶም በዙፋን ላይ ከተቀመጠ ከዚያ ከቀኝ እጁ መጽሐፉን ወሰደው።
8And when he took the scroll, the four living creatures and the twenty-four elders fell before the Lamb, having each one harps and golden vials full of perfumes, which are the prayers of the saints,
8መጽሐፉንም በወሰደ ጊዜ አራቱ እንስሶችና ሀያ አራቱ ሽማግሌዎች በበጉ ፊት ወደቁ፥ እያንዳንዳቸውም በገናንና የቅዱሳን ጸሎት የሆነ ዕጣን የሞላበትን የወርቅ ዕቃ ያዙ።
9and they sing a new song, saying, `Worthy art thou to take the scroll, and to open the seals of it, because thou wast slain, and didst redeem us to God in thy blood, out of every tribe, and tongue, and people, and nation,
9መጽሐፉን ትወስድ ዘንድ ማኅተሞቹንም ትፈታ ዘንድ ይገባሃል፥ ታርደሃልና፥ በደምህም ለእግዚአብሔር ከነገድ ሁሉ ከቋንቋም ሁሉ ከወገንም ሁሉ ከሕዝብም ሁሉ ሰዎችን ዋጅተህ ለአምላካችን መንግሥትና ካህናት ይሆኑ ዘንድ አደረግሃቸው፥ በምድርም ላይ ይነግሣሉ እያሉ አዲስን ቅኔ ይዘምራሉ።
10and didst make us to our God kings and priests, and we shall reign upon the earth.`
11አየሁም፥ በዙፋኑም በእንስሶቹም በሽማግሌዎቹም ዙሪያ የብዙ መላእክትን ድምፅ ሰማሁ፤ ቍጥራቸውም አእላፋት ጊዜ አእላፋትና ሺህ ጊዜ ሺህ ነበር፥
11And I saw, and I heard the voice of many messengers round the throne, and the living creatures, and the elders — and the number of them was myriads of myriads, and thousands of thousands —
12በታላቅም ድምፅ። የታረደው በግ ኃይልና ባለ ጠግነት ጥበብም ብርታትም ክብርም ምስጋናም በረከትም ሊቀበል ይገባዋል አሉ።
12saying with a great voice, `Worthy is the Lamb that was slain to receive the power, and riches, and wisdom, and strength, and honour, and glory, and blessing!`
13በሰማይና በምድርም ከምድርም በታች በባሕርም ላይ ያለ ፍጥረት ሁሉ በእነርሱም ውስጥ ያለ ሁሉ። በረከትና ክብር ምስጋናም ኃይልም ከዘላለም እስከ ዘላለም በዙፋኑ ላይ ለተቀመጠው፥ ለበጉም ይሁን ሲሉ ሰማሁ።
13and every creature that is in the heaven, and in the earth, and under the earth, and the things that are upon the sea, and the all things in them, heard I saying, `To Him who is sitting upon the throne, and to the Lamb, [is] the blessing, and the honour, and the glory, and the might — to the ages of the ages!`
14አራቱም እንስሶች። አሜን አሉ፥ ሽማግሌዎቹም ወድቀው ሰገዱ።
14and the four living creatures said, `Amen!` and the twenty-four elders fell down and they bow before Him who is living to the ages of the ages.