1And him who is weak in the faith receive ye — not to determinations of reasonings;
1በእምነት የደከመውንም ተቀበሉት፥ በአሳቡም ላይ አትፍረዱ።
2one doth believe that he may eat all things — and he who is weak doth eat herbs;
2ሁሉን ይበላ ዘንድ እንደ ተፈቀደለት የሚያምን አለ፥ ደካማው ግን አትክልት ይበላል።
3let not him who is eating despise him who is not eating: and let not him who is not eating judge him who is eating, for God did receive him.
3የሚበላ የማይበላውን አይናቀው የማይበላውም በሚበላው አይፍረድ፥ እግዚአብሔር ተቀብሎታልና።
4Thou — who art thou that art judging another`s domestic? to his own master he doth stand or fall; and he shall be made to stand, for God is able to make him stand.
4አንተ በሌላው ሎሌ የምትፈርድ ማን ነህ? እርሱ ቢቆም ወይም ቢወድቅ ለገዛ ጌታው ነው፤ ነገር ግን እግዚአብሔር ሊያቆመው ይችላልና ይቆማል።
5One doth judge one day above another, and another doth judge every day [alike]; let each in his own mind be fully assured.
5ይህ ሰው አንድ ቀን ከሌላ ቀን እንዲሻል ያስባል፥ ያ ግን ቀን ሁሉ አንድ እንደ ሆነ ያስባል፤ እያንዳንዱ በገዛ አእምሮው አጥብቆ ይረዳ።
6He who is regarding the day, to the Lord he doth regard [it], and he who is not regarding the day, to the Lord he doth not regard [it]. He who is eating, to the Lord he doth eat, for he doth give thanks to God; and he who is not eating, to the Lord he doth not eat, and doth give thanks to God.
6ቀንን የሚያከብር ለጌታ ብሎ ያከብራል፤ የሚበላም እግዚአብሔርን ያመሰግናልና ለጌታ ብሎ ይበላል፤ የማይበላም ለጌታ ብሎ አይበላም እግዚአብሔርንም ያመሰግናል።
7For none of us to himself doth live, and none to himself doth die;
7ከእኛ አንድ ስንኳ ለራሱ የሚኖር የለምና፥ ለራሱም የሚሞት የለም፤
8for both, if we may live, to the Lord we live; if also we may die, to the Lord we die; both then if we may live, also if we may die, we are the Lord`s;
8በሕይወት ሆነን ብንኖር ለጌታ እንኖራለንና፥ ብንሞትም ለጌታ እንሞታለን። እንግዲህ በሕይወት ሆነን ብንኖር ወይም ብንሞት የጌታ ነን።
9for because of this Christ both died and rose again, and lived again, that both of dead and of living he may be Lord.
9ስለዚህ ነገር ሙታንንም ሕያዋንንም ይገዛ ዘንድ ክርስቶስ ሞቶአልና ሕያውም ሆኖአልና።
10And thou, why dost thou judge thy brother? or again, thou, why dost thou set at nought thy brother? for we shall all stand at the tribunal of the Christ;
10አንተም በወንድምህ ላይ ስለ ምን ትፈርዳለህ? ወይስ አንተ ደግሞ ወንድምህን ስለ ምን ትንቃለህ? ሁላችን በክርስቶስ ፍርድ ወንበር ፊት እንቆማለንና።
11for it hath been written, `I live! saith the Lord — to Me bow shall every knee, and every tongue shall confess to God;`
11እኔ ሕያው ነኝ፥ ይላል ጌታ፥ ጉልበት ሁሉ ለእኔ ይንበረከካል መላስም ሁሉ እግዚአብሔርን ያመሰግናል ተብሎ ተጽፎአልና።
12so, then, each of us concerning himself shall give reckoning to God;
12እንግዲያስ እያንዳንዳችን ስለ ራሳችን ለእግዚአብሔር መልስ እንሰጣለን።
13no longer, therefore, may we judge one another, but this judge ye rather, not to put a stumbling-stone before the brother, or an offence.
13እንግዲህ ከዛሬ ጀምሮ እርስ በርሳችን አንፈራረድ፤ ይልቁን ግን ለወንድም እንቅፋትን ወይም ማሰናከያን ማንም እንዳያኖርበት ይህን ቍረጡ።
14I have known, and am persuaded, in the Lord Jesus, that nothing [is] unclean of itself, except to him who is reckoning anything to be unclean — to that one [it is] unclean;
14በራሱ ርኵስ የሆነ ነገር እንደ ሌለ በጌታ በኢየሱስ ሆኜ አውቄአለሁ ተረድቼአለሁም፤ ነገር ግን ምንም ርኵስ እንዲሆን ለሚቆጥር ለእርሱ ርኵስ ነው።
15and if through victuals thy brother is grieved, no more dost thou walk according to love; do not with thy victuals destroy that one for whom Christ died.
15ወንድምህንም በመብል ምክንያት የምታሳዝን ከሆንህ እንግዲህ በፍቅር አልተመላለስህም። ክርስቶስ ስለ እርሱ የሞተለትን እርሱን በመብልህ አታጥፋው።
16Let not, then, your good be evil spoken of,
16እንግዲህ ለእናንተ ያለው መልካም ነገር አይሰደብ፤
17for the reign of God is not eating and drinking, but righteousness, and peace, and joy in the Holy Spirit;
17የእግዚአብሔር መንግሥት ጽድቅና ሰላም በመንፈስ ቅዱስም የሆነ ደስታ ናት እንጂ መብልና መጠጥ አይደለችምና።
18for he who in these things is serving the Christ, [is] acceptable to God and approved of men.
18እንደዚህ አድርጎ ለክርስቶስ የሚገዛ እግዚአብሔርን ደስ ያሰኛልና፥ በሰውም ዘንድ የተመሰገነ ነው።
19So, then, the things of peace may we pursue, and the things of building up one another;
19እንግዲያስ ሰላም የሚቆምበትን እርስ በርሳችንም የምንታነጽበትን እንከተል።
20for the sake of victuals cast not down the work of God; all things, indeed, [are] pure, but evil [is] to the man who is eating through stumbling.
20በመብል ምክንያት የእግዚአብሔርን ሥራ አታፍርስ። ሁሉ ንጹሕ ነው፥ በመጠራጠር የተበላ እንደ ሆነ ግን ለዚያ ሰው ክፉ ነው።
21Right [it is] not to eat flesh, nor to drink wine, nor to [do anything] in which thy brother doth stumble, or is made to fall, or is weak.
21ሥጋን አለመብላት ወይንንም አለመጠጣት ወንድምህም የሚሰናከልበትን አለማድረግ መልካም ነው።
22Thou hast faith! to thyself have [it] before God; happy is he who is not judging himself in what he doth approve,
22ለአንተ ያለህ እምነት በእግዚአብሔር ፊት ለራስህ ይሁንልህ። ፈትኖ መልካም እንዲሆን በሚቈጥረው ነገር በራሱ ላይ የማይፈርድ ብፁዕ ነው።
23and he who is making a difference, if he may eat, hath been condemned, because [it is] not of faith; and all that [is] not of faith is sin.
23የሚጠራጠረው ግን ቢበላ በእምነት ስላልሆነ ተኮንኖአል፤ በእምነትም ያልሆነ ሁሉ ኃጢአት ነው።