Young`s Literal Translation

Amharic: New Testament

Romans

4

1What, then, shall we say Abraham our father, to have found, according to flesh?
1እንግዲህ በሥጋ አባታችን የሆነ አብርሃም ምን አገኘ እንላለን?
2for if Abraham by works was declared righteous, he hath to boast — but not before god;
2አብርሃም በሥራ ጸድቆ ቢሆን የሚመካበት አለውና፥ ነገር ግን በእግዚአብሔር ዘንድ አይደለም።
3for what doth the writing say? `And Abraham did believe God, and it was reckoned to him — to righteousness;`
3መጽሐፍስ ምን አለ? አብርሃምም እግዚአብሔርን አመነ ጽድቅም ሆኖ ተቈጠረለት።
4and to him who is working, the reward is not reckoned of grace, but of debt;
4ለሚሠራ ደመወዝ እንደ ዕዳ ነው እንጂ እንደ ጸጋ አይቈጠርለትም፤
5and to him who is not working, and is believing upon Him who is declaring righteous the impious, his faith is reckoned — to righteousness:
5ነገር ግን ለማይሠራ፥ ኃጢአተኛውንም በሚያደድቅ ለሚያምን ሰው እምነቱ ጽድቅ ሆኖ ይቆጠርለታል።
6even as David also doth speak of the happiness of the man to whom God doth reckon righteousness apart from works:
6እንደዚህ ዳዊት ደግሞ እግዚአብሔር ያለ ሥራ ጽድቅን ስለሚቆጥርለት ስለ ሰው ብፅዕና ይናገራል እንዲህ ሲል።
7`Happy they whose lawless acts were forgiven, and whose sins were covered;
7ዓመፃቸው የተሰረየላቸው ኃጢአታቸውም የተከደነላቸው ብፁዓን ናቸው፤
8happy the man to whom the Lord may not reckon sin.`
8ጌታ ኃጢአቱን የማይቆጥርበት ሰው ብፁዕ ነው።
9[Is] this happiness, then, upon the circumcision, or also upon the uncircumcision — for we say that the faith was reckoned to Abraham — to righteousness?
9እንግዲህ ይህ ብፅዕና ስለ መገረዝ ተነገረ? ወይስ ደግሞ ስለ አለመገረዝ? እምነቱ ለአብርሃም ጽድቅ ሆኖ ተቆጠረለት እንላለንና።
10how then was it reckoned? he being in circumcision, or in uncircumcision? not in circumcision, but in uncircumcision;
10እንዴት ተቆጠረለት? ተገርዞ ሳለ ነውን? ወይስ ሳይገረዝ? ተገርዞስ አይደለም፥ ሳይገረዝ ነበር እንጂ።
11and a sign he did receive of circumcision, a seal of the righteousness of the faith in the uncircumcision, for his being father of all those believing through uncircumcision, for the righteousness also being reckoned to them,
11ሳይገረዝም በነበረው እምነት ያገኘው የጽድቅ ማኅተም የሆነ የመገረዝን ምልክት ተቀበለ፤ ይህም እነርሱ ደግሞ ጻድቃን ሆነው ይቆጠሩ ዘንድ ሳይገረዙ ለሚያምኑ ሁሉ አባት እንዲሆን ነው፥
12and father of circumcision to those not of circumcision only, but who also walk in the steps of the faith, that [is] in the uncircumcision of our father Abraham.
12ለተገረዙትም አባት እንዲሆን ነው፤ ይኸውም ለተገረዙት ብቻ አይደለም ነገር ግን አባታችን አብርሃም ሳይገረዝ የነበረውን የእምነቱን ፍለጋ ደግሞ ለሚከተሉ ነው።
13For not through law [is] the promise to Abraham, or to his seed, of his being heir of the world, but through the righteousness of faith;
13የዓለምም ወራሽ እንዲሆን ለአብርሃምና ለዘሩ የተሰጠው የተስፋ ቃል በእምነት ጽድቅ ነው እንጂ በሕግ አይደለም።
14for if they who are of law [are] heirs, the faith hath been made void, and the promise hath been made useless;
14ከሕግ የሆኑትስ ወራሾች ከሆኑ እምነት ከንቱ ሆኖአል የተስፋውም ቃል ተሽሮአል፤
15for the law doth work wrath; for where law is not, neither [is] transgression.
15ሕጉ መቅሠፍትን ያደርጋልና፤ ነገር ግን ሕግ በሌለበት መተላለፍ የለም።
16Because of this [it is] of faith, that [it may be] according to grace, for the promise being sure to all the seed, not to that which [is] of the law only, but also to that which [is] of the faith of Abraham,
16ስለዚህ ከሕግ ብቻ ሳይሆን ከአብርሃም እምነት ደግሞ ለሆነ ለዘሩ ሁሉ የተስፋው ቃል እንዲጸና እንደ ጸጋ ይሆን ዘንድ በእምነት ነው፤ እርሱም። ለብዙ አሕዛብ አባት አደረግሁህ ተብሎ እንደ ተጻፈ፥ ለሙታን ሕይወት በሚሰጥ የሌለውንም እንዳለ አድርጎ በሚጠራ ባመነበት በአምላክ ፊት የሁላችን አባት ነው።
17who is father of us all (according as it hath been written — `A father of many nations I have set thee,`) before Him whom he did believe — God, who is quickening the dead, and is calling the things that be not as being.
18ዘርህ እንዲሁ ሊሆን ነው እንደ ተባለ፥ ተስፋ ባልሆነው ጊዜ የብዙ አሕዛብ አባት እንዲሆን ተስፋ ይዞ አመነ።
18Who, against hope in hope did believe, for his becoming father of many nations according to that spoken: `So shall thy seed be;`
19የመቶ ዓመትም ሽማግሌ ስለ ሆነ እንደ ምውት የሆነውን የራሱን ሥጋና የሳራ ማኅፀን ምውት መሆኑን በእምነቱ ሳይደክም ተመለከተ፤
19and not having been weak in the faith, he did not consider his own body, already become dead, (being about a hundred years old,) and the deadness of Sarah`s womb,
20ለእግዚአብሔርም ክብር እየሰጠ፥ የሰጠውንም ተስፋ ደግሞ ሊፈጽም እንዲችል አጥብቆ እየተረዳ፥ በእምነት በረታ እንጂ በአለማመን ምክንያት በእግዚአብሔር ተስፋ ቃል አልተጠራጠረም።
20and at the promise of God did not stagger in unbelief, but was strengthened in faith, having given glory to God,
22ስለዚህ ደግሞ ጽድቅ ሆኖ ተቆጠረለት።
21and having been fully persuaded that what He hath promised He is able also to do:
23ነገር ግን። ተቈጠረለት የሚለው ቃል ስለ እርሱ ብቻ የተጻፈ አይደለም፥ ስለ እኛም ነው እንጂ፤
22wherefore also it was reckoned to him to righteousness.
24ስለ በደላችን አልፎ የተሰጠውን እኛን ስለ ማጽደቅም የተነሣውን ጌታንችንን ኢየሱስን ከሙታን ባስነሣው ለምናምን ለእኛ ይቈጠርልን ዘንድ አለው።
23And it was not written on his account alone, that it was reckoned to him,
24but also on ours, to whom it is about to be reckoned — to us believing on Him who did raise up Jesus our Lord out of the dead,
25who was delivered up because of our offences, and was raised up because of our being declared righteous.