Amharic: New Testament

聖經新譯本

1 Corinthians

14

1ፍቅርን ተከታተሉ፥ መንፈሳዊ ስጦታንም ይልቁንም ትንቢት መናገርን በብርቱ ፈልጉ።
1講道與說方言的恩賜你們要追求愛,也要熱切地渴慕屬靈的恩賜,特別是先知講道的恩賜。
2በልሳን የሚናገርስ ለእግዚአብሔር እንጂ ለሰው አይናገርም፤ የሚያስተውለው የለምና፥ በመንፈስ ግን ምሥጢርን ይናገራል፤
2原來那說方言的不是對人說,而是對 神說,因為沒有人能聽得懂;他是在靈裡講奧祕的事。
3ትንቢትን የሚናገር ግን ለማነጽና ለመምከር ለማጽናናትም ለሰው ይናገራል።
3但那講道的是對人講說,使他們得著造就、安慰和勸勉。
4በልሳን የሚናገር ራሱን ያንጻል፤ ትንቢትን የሚናገር ግን ማኅበሩን ያንጻል።
4那說方言的是造就自己,但那講道的是造就教會。
5ሁላችሁ በልሳኖች ልትናገሩ እወድ ነበር፥ ትንቢትን ልትናገሩ ግን ከዚህ ይልቅ እወዳለሁ፤ ማኅበሩ ይታነጽ ዘንድ ንግግሩን ባይተረጐም በልሳኖች ከሚናገር ትንቢትን የሚናገር ይበልጣል።
5我願意你們都說方言,但我更願意你們都講道;因為那說方言的,如果不翻譯出來使教會得著造就,就遠不如那講道的了。
6አሁን ግን፥ ወንድሞች ሆይ፥ ወደ እናንተ መጥቼ በልሳኖች ብናገር፥ በመግለጥ ወይም በእውቀት ወይም በትንቢት ወይም በትምህርት ካልነገርኋችሁ ምን እጠቅማችኋለሁ?
6弟兄們,你們想想,如果我到你們那裡去,只說方言,不向你們講有關啟示、知識、預言,或教訓的話,那我對你們有甚麼益處呢?
7ነፍስ የሌለበት ነገር እንኳ ዋሽንትም ክራርም ቢሆን ድምፅ ሲሰጥ የድምፁን ልዩነት ባይገልጥ በዋሽንት የሚነፋው ወይስ በክራር የሚመታው መዝሙር እንዴት ይታወቃል?
7甚至那些沒有生命卻能發聲的東西,例如簫或琴,如果音調不分,怎能使人知道所彈所奏的是甚麼呢?
8ደግሞም መለከት የማይገለጥን ድምፅ ቢሰጥ ለጦርነት ማን ይዘጋጃል?
8又如果軍號所發的聲音不清楚,誰會準備作戰呢?
9እንዲሁ እናንተ ደግሞ የተገለጠውን ቃል በአንደበት ባትናገሩ ሰዎች የምትናገሩትን እንዴት አድርገው ያስተውሉታል? ለነፋስ የምትናገሩ ትሆናላችሁና።
9你們也是這樣,如果用舌頭發出人聽不懂的話來,人怎會知道你所講的是甚麼呢?這樣,你們就是向空氣說話了。
10በዓለም ምናልባት ቁጥር የሌለው የቋንቋ ዓይነት ይኖራል ቋንቋም የሌለው ሕዝብ የለም፤
10世上有那麼多種語言,但沒有一種是沒有意義的。
11እንግዲህ የቋንቋውን ፍች ባላውቅ ለሚናገረው እንግዳ እሆናለሁ፥ የሚናገረውም ለእኔ እንግዳ ይሆናል።
11我若不明白某一種語言的意思,在那講的人來看,我就是個外國人;在我來說,那講話的人也是個外國人。
12እንዲሁ ደግሞ እናንተ መንፈሳዊ ስጦታን በብርቱ የምትፈልጉ ከሆናችሁ ቤተ ክርስቲያንን ለማነጽ እንዲበዛላችሁ ፈልጉ።
12你們也是這樣,你們既然熱切地渴慕屬靈的恩賜,就應當追求多多得著造就教會的恩賜。
13ስለዚህ በልሳን የሚናገር እንዲተረጉም ይጸልይ።
13所以,說方言的應當祈求,使他能把方言翻譯出來。
14በልሳን ብጸልይ መንፈሴ ይጸልያል አእምሮዬ ግን ያለ ፍሬ ነው።
14我若用方言禱告,是我的靈在禱告,我的理智並沒有作用。
15እንግዲህ ምንድር ነው? በመንፈስ እጸልያለሁ በአእምሮም ደግሞ እጸልያለሁ፤ በመንፈስ እዘምራለሁ በአእምሮም ደግሞ እዘምራለሁ።
15那麼我應當怎樣行呢?我要用靈禱告,也要用理智禱告;我要用靈歌唱,也要用理智歌唱。
16እንዲያማ ካልሆነ፥ አንተ በመንፈስ ብትባርክ ባልተማሩት ስፍራ የተቀመጠው የምትለውን ካላወቀ እንዴት አድርጎ ለምስጋናህ አሜን ይላል?
16不然,如果你用靈讚美,在場那些不明白的人,因為不知道你在說甚麼,怎能在你感謝的時候說“阿們”呢?
17አንተማ መልካም ታመሰግናለህ፥ ሌላው ግን አይታነጽበትም።
17你感謝固然是好,但別人卻得不著造就。
18ከሁላችሁ ይልቅ በልሳኖች እናገራለሁና እግዚአብሔርን አመሰግናለሁ፤
18我感謝 神,我說方言比你們大家都多。
19ነገር ግን ሌሎችን ደግሞ አስተምር ዘንድ በማኅበር እልፍ ቃላት በልሳን ከመናገር ይልቅ አምስት ቃላት በአእምሮዬ ልናገር እወዳለሁ።
19但在教會中,我寧願用理智說五句話去教導人,勝過用方言說萬句話。
20ወንድሞች ሆይ፥ በአእምሮ ሕፃናት አትሁኑ፤ ለክፋት ነገር ሕፃናት ሁኑ እንጂ በአእምሮ የበሰሉ ሁኑ።
20弟兄們,你們在思想上不要作小孩子,卻要在惡事上作嬰孩,在思想上作成年人。
21ሌሎችን ልሳኖች በሚናገሩ ሰዎችና በሌላ አንደበት ለዚህ ሕዝብ እነግራቸዋለሁ፥ እንዲህም ቢሆን አይሰሙኝም ይላል ጌታ ተብሎ በሕግ ተጽፎአል።
21律法上記著說:“主說:我要藉著說別種話的人,用外國人的嘴唇,對這人民說話;雖然這樣,他們還是不聽我。”
22እንግዲያስ በልሳኖች መናገር ለማያምኑ ምልክት ነው እንጂ ለሚያምኑ አይደለም፥ ትንቢት ግን ለሚያምኑ እንጂ ለማያምኑ አይደለም።
22可見說方言不是要給信主的人作記號,而是要給未信的人;講道不是要給未信的人,而是要給信主的人作記號。
23እንግዲህ ማኅበር ሁሉ አብረው ቢሰበሰቡ ሁሉም በልሳኖች ቢናገሩና ያልተማሩ ወይም የማያምኑ ሰዎች ቢገቡ። አብደዋል አይሉምን?
23所以,如果全教會聚在一起的時候,大家都說方言,有不明白的人或未信的人進來,不是要說你們瘋了嗎?
24ሁሉ ትንቢት ቢናገሩ ግን የማያምን ወይም ያልተማረ ሰው ቢገባ በሁሉ ይወቀሳል፥ በሁሉም ይመረመራል፤
24如果大家都講道,有未信的人或不明白的人進來,他就會被眾人勸服而知罪,被眾人審問了。
25በልቡም የተሰወረ ይገለጣል እንዲሁም። እግዚአብሔር በእውነት በመካከላቸው ነው ብሎ እየተናገረ በፊቱ ወድቆ ለእግዚአብሔር ይሰግዳል።
25他心裡隱祕的事被顯露出來,他就必俯伏敬拜 神,宣告說:“ 神真的是在你們中間了。”
26እንግዲህ፥ ወንድሞች ሆይ፥ ምንድር ነው? በምትሰበሰቡበት ጊዜ ለእያንዳንዱ መዝሙር አለው፥ ትምህርት አለው፥ መግለጥ አለው፥ በልሳን መናገር አለው፥ መተርጐም አለው፤ ሁሉ ለማነጽ ይሁን።
26 神不是混亂而是和平的弟兄們,那麼應該怎麼辦呢?你們聚集在一起的時候,各人或有詩歌,或有教訓,或有啟示,或有方言,或有翻譯出來的話,一切都應該能造就人。
27በልሳን የሚናገር ቢኖር ሁለት ወይም ቢበዛ ሦስት ሆነው በተራቸው ይናገሩ አንዱም ይተርጉም፤
27如果有人說方言,只可以有兩個人,或最多三個人,並且要輪流說,同時要有一個人翻譯。
28የሚተረጉም ባይኖር ግን በማኅበር መካከል ዝም ይበልና ለራሱና ለእግዚአብሔር ይናገር።
28如果沒有人翻譯,他就應當在會中閉口,只對自己和對 神說好了。
29ነቢያትም ሁለት ወይም ሦስት ሆነው ይናገሩ ሌሎችም ይለዩአቸው፤
29講道的,也只可以兩三個人講,其餘的人要衡量他們所講的。
30በዚያ ለሚቀመጥ ለሌላ ግን አንድ ነገር ቢገለጥለት ፊተኛው ዝም ይበል።
30在座的有人得了啟示,那先講的人就應當住口。
31ሁሉም እንዲማሩ ሁሉም እንዲመከሩ ሁላችሁ በእያንዳንዳችሁ ትንቢት ልትናገሩ ትችላላችሁ።
31因為你們都可以輪流講道,好讓大家都可以學習,都可以得到勉勵。
32የነቢያትም መናፍስት ለነቢያት ይገዛሉ፤
32先知的靈是受先知控制的,
33እግዚአብሔርስ የሰላም አምላክ ነው እንጂ የሁከት አምላክ አይደለምና፤ በቅዱሳንም አብያተ ክርስቲያናት ሁሉ እንዲህ ነው።
33因為 神不是混亂的,而是和平的。
34ሴቶች በማኅበር ዝም ይበሉ፤ ሕግ ደግሞ እንደሚል እንዲገዙ እንጂ እንዲናገሩ አልተፈቀደላቸውምና።
34婦女在聚會中應當閉口,好像在聖徒的眾教會中一樣,因為她們是不准講話的;就如律法所說的,她們應該順服。
35ለሴት በማኅበር መካከል መናገር ነውር ነውና፥ ምንም ሊማሩ ቢወዱ በቤታቸው ባሎቻቸውን ይጠይቁ።
35如果她們想要學甚麼,可以在家裡問自己的丈夫,因為婦女在聚會中講話原是可恥的。
36ምን ነው? የእግዚአብሔር ቃል የወጣ ከእናንተ ነውን? ወይስ ወደ እናንተ ብቻ ደርሶአልን?
36難道 神的道是從你們出來的嗎?是單單臨到你們的嗎?
37ማንም ነቢይ ወይም መንፈሳዊ የሆነ ቢመስለው ይህች የጻፍሁላችሁ የጌታ ትእዛዝ እንደ ሆነች ይወቅ፤
37如果有人自以為是先知或是屬靈的,他就應該知道我寫給你們的是主的命令;
38ማንም የማያውቅ ቢኖር ግን አይወቅ።
38如果有人不理會,別人也不必理會他。
39ስለዚህ፥ ወንድሞች ሆይ፥ ትንቢት ለመናገር በብርቱ ፈልጉ፥ በልሳኖች ከመናገርም አትከልክሉ፤
39所以我的弟兄們,你們要熱切地追求講道的恩賜,也不要禁止說方言。
40ነገር ግን ሁሉ በአገባብና በሥርዓት ይሁን።
40凡事都要規規矩矩地按著次序行。