Amharic: New Testament

聖經新譯本

2 Corinthians

2

1ነገር ግን ዳግመኛ በኀዘን ወደ እናንተ እንዳልመጣ ስለ እኔ ቆረጥሁ።
1我自己決定了,到你們那裡去的時候,不再是憂愁的。
2እኔስ ባሳዝናችሁ፥ እንግዲያስ በእኔ ምክንያት ከሚያዝን በቀር ደስ የሚያሰኘኝ ማን ነው?
2如果我使你們憂愁,除了那因我而憂愁的人以外,誰能使我快樂呢?
3ደስ ሊያሰኙኝ ከሚገባቸውም በመምጣቴ ኀዘን እንዳይሆንብኝ ይህንኑ ጻፍሁላችሁ፥ ደስታዬ የሁላችሁ ደስታ ነው ብዬ በሁላችሁ ታምኜአለሁና።
3我寫了這樣的信,免得我來的時候,應該使我快樂的人反而使我憂愁;我深信你們眾人都以我的喜樂為你們的喜樂。
4በብዙ መከራና ከልብ ጭንቀት በብዙም እንባ ጽፌላችሁ ነበርና፤ ይህም እናንተን አብዝቼ የምወድበትን ፍቅር እንድታውቁ እንጂ እንዳሳዝናችሁ አይደለም።
4我從前心裡痛苦難過,流著眼淚寫信給你們,並不是要使你們憂愁,而是要你們知道我是多麼愛你們。
5ነገር ግን ማንም አሳዝኖ ቢሆን፥ እንዳልከብድባችሁ፥ በክፍል ሁላችሁን እንጂ እኔን ያሳዘነ አይደለም።
5饒恕犯罪的弟兄如果有人使人憂愁,他不是使我憂愁,而是使你們眾人都有一點憂愁;我只說有一點,是避免說得過分。
6እንደዚህ ላለ ሰው ይህ ከእናንተ የምትበዙት የቀጣችሁት ቅጣት ይበቃዋልና እንደዚህ ያለው ከልክ በሚበዛ ኀዘን እንዳይዋጥ፥
6這樣的人受了許多人的責備,也就夠了,
7ይልቅ ተመልሳችሁ ይቅር ማለትና ማጽናናት ይገባችኋል።
7倒不如饒恕他,安慰他,免得他因憂愁過度而受不了。
8ስለዚህ ከእርሱ ጋር ፍቅርን እንድታጸኑ እለምናችኋለሁ፤
8所以,我勸你們要向他確實顯明你們的愛心。
9ስለዚህ ደግሞ ጽፌ ነበርና፤ በሁሉ የምትታዘዙ እንደ ሆናችሁ የእናንተን መፈተን አውቅ ዘንድ አሳቤ ነበር።
9為這緣故,我寫了那封信,要考驗你們是不是凡事都順從。
10እናንተ ግን ይቅር የምትሉትን እኔ ደግሞ ይቅር እለዋለሁ፤ እኔም ይቅር ካልሁ፥ ይቅር ያልሁትን ስለ እናንተ በክርስቶስ ፊት ይቅር ብዬአለሁ፥
10你們饒恕誰,我也饒恕誰;我所饒恕了的(如果我饒恕過甚麼),是為了你們在基督面前饒恕的,
11በሰይጣን እንዳንታለል፤ የእርሱን አሳብ አንስተውምና።
11免得撒但有機可乘,因為我們並不是不曉得他的詭計。
12ስለ ክርስቶስም ወንጌል ወደ ጢሮአዳ በመጣሁ ጊዜ፥ ለጌታ ሥራ በር ምንም ቢከፈትልኝ፥ ቲቶን ወንድሜን ስላላገኘሁት መንፈሴ ዕረፍት አልነበረውም፥
12基督的馨香從前我為基督的福音到了特羅亞,雖然主給我開了門,
13ነገር ግን ከእነርሱ ተሰናብቼ ወደ መቄዶንያ ወጣሁ።
13我心裡仍然沒有安寧,因為見不到提多弟兄。於是我辭別了那裡的人,到馬其頓去了。
14ነገር ግን በክርስቶስ ሁልጊዜ ድል በመንሣቱ ለሚያዞረን በእኛም በየስፍራው ሁሉ የእውቀቱን ሽታ ለሚገልጥ ለአምላክ ምስጋና ይሁን፤
14感謝 神,他常常在基督裡,使我們這些作俘虜的,列在凱旋的隊伍當中,又藉著我們在各地散播香氣,就是使人認識基督。
15በሚድኑቱና በሚጠፉቱ ዘንድ ለእግዚአብሔር የክርስቶስ መዓዛ ነንና፤
15因為無論在得救的人或滅亡的人中間,我們都是基督的馨香,是獻給 神的。
16ለእነዚህ ለሞት የሚሆን የሞት ሽታ ለእነዚያም ለሕይወት የሚሆን የሕይወት ሽታ ነን። ለዚህም ነገር የሚበቃ ማን ነው?
16對於滅亡的人,這是死亡的氣味叫人死;對於得救的人,這卻是生命的香氣使人活。這些事誰夠資格作呢?
17የእግዚአብሔርን ቃል ቀላቅለው እንደሚሸቃቅጡት እንደ ብዙዎቹ አይደለንምና፤ በቅንነት ግን ከእግዚአብሔር እንደ ተላክን በእግዚአብሔር ፊት በክርስቶስ ሆነን እንናገራለን።
17我們不像那許多的人,為了圖利而謬講 神的道。相反地,我們講話,是出於真誠,出於 神,是在 神面前、在基督裡的。