Amharic: New Testament

聖經新譯本

2 Corinthians

4

1ስለዚህ ምክንያት ምሕረት እንደ ተሰጠን መጠን ይህ አገልግሎት ስላለን አንታክትም።
1新約的僕役所以,我們既然蒙了憐憫,得著這職分,就不沮喪,
2ነገር ግን የሚያሳፍረውን ስውር ነገር ጥለናልና በተንኮል አንመላለስም የእግዚአብሔርንም ቃል በውሸት አንቀላቅልም፤ እውነትን በመግለጥ ግን በእግዚአብሔር ፊት ለሰው ሕሊና ሁሉ ራሳችንን እናመሰግናለን።
2卻把暗昧可恥的事棄絕了;不行詭詐,不摻混 神的道,反而藉著顯揚真理,在 神面前把自己推薦給眾人的良心。
3ወንጌላችን የተከደነ ቢሆን እንኳ የተከደነባቸው ለሚጠፉ ነው።
3如果我們的福音被蒙蔽了,那是對滅亡的人才蒙蔽的。
4ለእነርሱም የእግዚአብሔር ምሳሌ የሆነ የክርስቶስ የክብሩ ወንጌል ብርሃን እንዳያበራላቸው፥ የዚህ ዓለም አምላክ የማያምኑትን አሳብ አሳወረ።
4這些不信的人被這世代的神弄瞎了他們的心眼,使他們看不見基督榮耀的福音的光;基督就是 神的形象。
5ክርስቶስ ኢየሱስን ጌታ እንደ ሆነ እንጂ ራሳችንን አንሰብክምና፥ ስለ ኢየሱስም ራሳችንን ለእናንተ ባሪያዎች እናደርጋለን።
5我們並不是傳揚自己,而是傳揚耶穌基督是主,並且為了耶穌的緣故成了你們的僕人。
6በክርስቶስ ፊት የእግዚአብሔርን የክብሩን እውቀት ብርሃን እንዲሰጥ በልባችን ውስጥ የበራ። በጨለማ ብርሃን ይብራ ያለ እግዚአብሔር ነውና።
6因為那說“要有光從黑暗裡照出來”的 神,已經照在我們的心裡,要我們把 神的榮光照出去,就是使人可以認識那在基督臉上的榮光。
7ነገር ግን የኃይሉ ታላቅነት ከእግዚአብሔር እንጂ ከእኛ እንዳይሆን ይህ መዝገብ በሸክላ ዕቃ ውስጥ አለን፤
7我們有這寶貝在瓦器裡,是要顯明這極大的能力是屬於 神,不是出於我們。
8በሁሉ እንገፋለን እንጂ አንጨነቅም፤ እናመነታለን እንጂ ተስፋ አንቆርጥም፤
8我們雖然四面受壓,卻沒有壓碎;心裡作難,卻不至絕望,
9እንሰደዳለን እንጂ አንጣልም፤ እንወድቃለን እንጂ አንጠፋም፤
9受到迫害,卻沒有被丟棄;打倒了,卻不至死亡。
10የኢየሱስ ሕይወት ደግሞ በሥጋችን ይገለጥ ዘንድ ሁልጊዜ የኢየሱስን መሞት በሥጋችን ተሸክመን እንዞራለን።
10我們身上常常帶著耶穌的死,好讓耶穌的生也在我們的身上顯明出來。
11የኢየሱስ ሕይወት ደግሞ በሚሞት ሥጋችን ይገለጥ ዘንድ እኛ ሕያዋን የሆንን ከኢየሱስ የተነሣ ዘወትር ለሞት አልፈን እንሰጣለንና።
11我們這些活著的人,為耶穌的緣故常常被人置於死地,好讓耶穌的生也在我們必死的身上顯明出來。
12ስለዚህ ሞቱ በእኛ ሕይወቱም በእናንተ ይሠራል።
12這樣看來,死在我們身上運行,生卻在你們的身上運行。
13ነገር ግን። አመንሁ ስለዚህም ተናገርሁ ተብሎ እንደ ተጻፈ ያው አንዱ የእምነት መንፈስ ስላለን፥ እኛ ደግሞ እናምናለን ስለዚህም እንናገራለን፤
13經上記著說:“我信,所以我說話。”我們既然有同樣的信心(“信心”原文作“信心的靈”),也就信,所以也說話,
14ጌታን ኢየሱስን ያስነሣው እኛን ደግሞ ከኢየሱስ ጋር እንዲያስነሣን ከእናንተም ጋር እንዲያቀርበን እናውቃለንና።
14因為知道那使主耶穌復活的,也必定使我們與耶穌一同復活,並且把我們和你們呈獻在他的面前。
15በብዙዎች በኩል የተትረፈረፈው ጸጋ ለእግዚአብሔር ክብር ምስጋናን ያበዛ ዘንድ፥ ሁሉ ስለ እናንተ ነውና።
15這一切都是為了你們,好使恩惠既然因著許多人而增多,感恩的心也更加增多了,使榮耀歸給 神。
16ስለዚህም አንታክትም፥ ነገር ግን የውጭው ሰውነታችን ቢጠፋ እንኳ የውስጡ ሰውነታችን ዕለት ዕለት ይታደሳል።
16日日更新所以,我們並不沮喪,我們外面的人雖然漸漸朽壞,但裡面的人卻日日更新,
17የማይታየውን እንጂ የሚታየውን ባንመለከት፥ ቀላል የሆነ የጊዜው መከራችን የክብርን የዘላለም ብዛት ከሁሉ መጠን ይልቅ ያደርግልናልና፤ የሚታየው የጊዜው ነውና፥ የማይታየው ግን የዘላለም ነው።
17因為我們短暫輕微的患難,是要為我們成就極大無比、永遠的榮耀。
18我們所顧念的,不是看得見的,而是看不見的;因為看得見的是暫時的,看不見的是永遠的。