Amharic: New Testament

聖經新譯本

Acts

11

1ሐዋርያትና በይሁዳም የነበሩት ወንድሞች አሕዛብ ደግሞ የእግዚአብሔርን ቃል እንደ ተቀበሉ ሰሙ።
1彼得向耶路撒冷教會報告使徒和在猶太的弟兄們,聽說外族人也接受了 神的道。
2ጴጥሮስም ወደ ኢየሩሳሌም በወጣ ጊዜ ከተገረዙት ወገን የሆኑት ሰዎች ከእርሱ ጋር ተከራክረው።
2彼得上到耶路撒冷的時候,那些守割禮的人與他爭論,
3ወዳልተገረዙ ሰዎች ገብተህ ከእነርሱ ጋር በላህ አሉት።
3說:“你竟然到未受割禮的人那裡,跟他們一起吃飯!”
4ጴጥሮስ ግን ከመጀመሪያው ጀምሮ በተራ ገለጠላቸው እንዲህም አለ።
4彼得就按著次序向他們講解,說:
5እኔ በኢዮጴ ከተማ ስጸልይ ሳለሁ ተመስጬ ራእይን አየሁ፤ ታላቅ ሸማ የመሰለ ዕቃ በአራት ማዕዘን ተይዞ ከሰማይ ወረደና ወደ እኔ መጣ፤
5“我在約帕城禱告的時候,魂遊象外,見到異象:有一件東西,好像一塊大布,綁著四角,從天上降下來,一直來到我面前。
6ይህንም ትኵር ብዬ ስመለከት አራት እግር ያላቸውን የምድር እንስሶች አራዊትንም ተንቀሳቃሾችንም የሰማይ ወፎችንም አየሁ።
6我定睛觀察,看見裡面有地上的四足牲畜、走獸,還有昆蟲和天空的飛鳥。
7ጴጥሮስ ሆይ፥ ተነሣና አርደህ ብላ የሚለኝንም ድምፅ ሰማሁ።
7我也聽見有聲音對我說:‘彼得,起來,宰了吃!’
8እኔም። ጌታ ሆይ፥ አይሆንም፤ ርኵስ ወይም የሚያስጸይፍ ከቶ ወደ አፌ ገብቶ አያውቅምና አልሁ።
8我說:‘主啊,千萬不可,因為俗物或不潔的東西,從來沒有進過我的口。’
9ሁለተኛም። እግዚአብሔር ያነጻውን አንተ አታርክሰው የሚል ድምፅ ከሰማይ መለሰልኝ።
9第二次又有聲音從天上回答:‘ 神所潔淨的,你不可當作俗物。’
10ይህም ሦስት ጊዜ ሆነ እንደ ገናም ሁሉ ወደ ሰማይ ተሳበ።
10這樣一連三次之後,所有的東西都拉回天上去了。
11እነሆም፥ ያን ጊዜ ሦስት ሰዎች ከቂሣርያ ወደ እኔ ተልከው ወዳለሁበት ቤት ቀረቡ።
11就在那個時候,有三個從該撒利亞派到我這裡來的人,站在我住的房子門前。
12መንፈስም ሳልጠራጠር ከእነርሱ ጋር እሄድ ዘንድ ነገረኝ። እነዚህም ስድስቱ ወንድሞች ደግሞ ከእኔ ጋር መጡ ወደዚያ ሰውም ቤት ገባን።
12聖靈吩咐我跟他們一起去,一點也不要疑惑。這六位弟兄也跟我一起去,我們就進了那人的家。
13እርሱም መልአክ በቤቱ ቆሞ እንዳየና። ወደ ኢዮጴ ሰዎች ልከህ ጴጥሮስ የተባለውን ስምዖንን አስመጣ፤
13他告訴我們,他怎樣看見天使站在他家裡說:‘派人到約帕去,請那個名叫彼得的西門來,
14እርሱም አንተና የቤትህ ሰዎች ሁሉ የምትድኑበትን ነገር ይነግርሃል እንዳለው ነገረን።
14他有話要告訴你,使你和你全家都可以得救。’
15ለመናገርም በጀመርሁ ጊዜ መንፈስ ቅዱስ ለእኛ ደግሞ በመጀመሪያ እንደ ወረደ ለእነርሱ ወረደላቸው።
15我一開始講話,聖靈就降在他們身上,正像當初降在我們身上一樣。
16ዮሐንስ በውኃ አጠመቀ እናንተ ግን በመንፈስ ቅዱስ ትጠመቃላችሁ ያለውም የጌታ ቃል ትዝ አለኝ።
16我就想起主所說的話:‘約翰用水施洗,但你們要受聖靈的洗。’
17እንግዲህ እግዚአብሔር በጌታ በኢየሱስ ክርስቶስ ላመነው ለእኛ ደግሞ እንደ ሰጠን ያን ስጦታ ለእነርሱ ከሰጠ፥ እግዚአብሔርን ለመከልከል እችል ዘንድ እኔ ማን ነበርሁ?
17 神既然把同樣的恩賜給他們,像給我們這些信了主耶穌基督的人一樣,我是誰,我能夠阻止 神嗎?”
18ይህን በሰሙ ጊዜም ዝም አሉና። እንኪያስ እግዚአብሔር ለአሕዛብ ደግሞ ለሕይወት የሚሆን ንስሐን ሰጣቸው እያሉ እግዚአብሔርን አከበሩ።
18眾人聽見這些話,就默然無聲,把榮耀歸給 神,說:“這樣看來, 神也把悔改的心賜給外族人,使他們得生命。”
19በእስጢፋኖስም ላይ በተደረገው መከራ የተበተኑት እስከ ፊንቄ እስከ ቆጵሮስም እስከ አንጾኪያም ድረስ ዞሩ፥ ቃሉንም ለአይሁድ ብቻ እንጂ ለአንድ ስንኳ አይናገሩም ነበር።
19安提阿的教會那些因司提反事件遭受苦難而四散的門徒,一直走到腓尼基、塞浦路斯、安提阿;他們不對別人傳講,只對猶太人傳講。
20ከእነርሱ ግን የቆጵሮስና የቀሬና ሰዎች የነበሩት አንዳንዶቹ ወደ አንጾኪያ መጥተው የጌታን የኢየሱስን ወንጌል እየሰበኩ ለግሪክ ሰዎች ተናገሩ።
20但其中有些塞浦路斯人和古利奈人,來到安提阿,也對希臘人傳講主耶穌。
21የጌታም እጅ ከእነርሱ ጋር ነበረ፤ ቍጥራቸውም እጅግ የሚሆን ሰዎች አምነው ወደ ጌታ ዘወር አሉ።
21主的手與他們同在,信而歸主的人就多起來。
22ወሬውም በኢየሩሳሌም ባለችው ቤተ ክርስቲያን ስለ እነርሱ ተሰማ፥ በርናባስንም ወደ አንጾኪያ ላኩት፤
22這事傳到耶路撒冷教會的耳中,他們就派巴拿巴到安提阿去。
23እርሱም መጥቶ የእግዚአብሔርን ጸጋ ባየ ጊዜ ደስ አለው፥ ሁሉንም በልባቸው ፈቃድ በጌታ ጸንተው ይኖሩ ዘንድ መከራቸው፤
23他到了那裡,看見 神所施的恩,就很歡喜,勸勉眾人堅心靠主。
24ደግ ሰውና መንፈስ ቅዱስ እምነትም የሞላበት ነበረና። ብዙ ሕዝብም ወደ ጌታ ተጨመሩ።
24巴拿巴是個好人,滿有聖靈和信心,於是許多人歸了主。
25በርናባስም ሳውልን ሊፈልግ ወደ ጠርሴስ መጣ፤
25後來他到大數去找掃羅,
26ባገኘውም ጊዜ ወደ አንጾኪያ አመጣው። በቤተ ክርስቲያንም አንድ ዓመት ሙሉ ተሰበሰቡ፥ ብዙ ሕዝብንም አስተማሩ፤ ደቀ መዛሙርትም መጀመሪያ በአንጾኪያ ክርስቲያን ተባሉ።
26找到了,就帶他來安提阿。足足有一年,他們一同在教會聚集,教導了許多人。門徒稱為基督徒,是從安提阿開始的。
27በዚያም ወራት ነቢያት ከኢየሩሳሌም ወደ አንጾኪያ ወረዱ፤
27那時,有幾位先知從耶路撒冷下到安提阿。
28ከእነርሱም አጋቦስ የሚሉት አንድ ሰው ተነሥቶ በዓለም ሁሉ ታላቅ ራብ ሊሆን እንዳለው በመንፈስ አመለከተ፤ ይህም በቀላውዴዎስ ቄሣር ዘመን ሆነ።
28其中有一個名叫亞迦布的站起來,藉著聖靈指出天下將要有大饑荒;這事在革老丟時期果然發生了。
29ደቀ መዛሙርትም እያንዳንዳቸው እንደ ችሎታቸው መጠን አዋጥተው በይሁዳ ለሚኖሩት ወንድሞች እርዳታን ይልኩ ዘንድ ወሰኑ፤
29於是門徒決定按著各人的力量捐款,好送給住在猶太的弟兄。
30እንዲህም ደግሞ አደረጉ፥ በበርናባስና በሳውልም እጅ ወደ ሽማግሌዎቹ ሰደዱት።
30他們就這樣行了,由巴拿巴和掃羅經手送到長老們那裡。