Amharic: New Testament

聖經新譯本

John

3

1ከፈሪሳውያንም ወገን የአይሁድ አለቃ የሆነ ኒቆዲሞስ የሚባል አንድ ሰው ነበረ፤ እርሱም በሌሊት ወደ ኢየሱስ መጥቶ።
1人必須重生有一個法利賽人,名叫尼哥德慕,是猶太人的官長。
2መምህር ሆይ፥ እግዚአብሔር ከእርሱ ጋር ከሆነ በቀር አንተ የምታደርጋቸውን እነዚህን ምልክቶች ሊያደርግ የሚችል የለምና መምህር ሆነህ ከእግዚአብሔር ዘንድ እንደ መጣህ እናውቃለን አለው።
2他夜間來到耶穌那裡,對他說:“拉比,我們知道你是從 神那裡來的教師,因為如果沒有 神同在,你所行的這些神蹟,就沒有人能行。”
3ኢየሱስም መልሶ። እውነት እውነት እልሃለሁ፥ ሰው ዳግመኛ ካልተወለደ በቀር የእግዚአብሔርን መንግሥት ሊያይ አይችልም አለው።
3耶穌回答:“我實實在在告訴你,人若不重生,就不能見 神的國。”
4ኒቆዲሞስም። ሰው ከሸመገለ በኋላ እንዴት ሊወለድ ይችላል? ሁለተኛ ወደ እናቱ ማኅፀን ገብቶ ይወለድ ዘንድ ይችላልን? አለው።
4尼哥德慕說:“人老了,怎能重生呢?難道他能再進母腹生出來嗎?”
5ኢየሱስም መለሰ፥ እንዲህ ሲል። እውነት እውነት እልሃለሁ፥ ሰው ከውኃና ከመንፈስ ካልተወለደ በቀር ወደ እግዚአብሔር መንግሥት ሊገባ አይችልም።
5耶穌回答:“我實實在在告訴你,人若不是從水和聖靈生的,就不能進 神的國。
6ከሥጋ የተወለደ ሥጋ ነው፥ ከመንፈስም የተወለደ መንፈስ ነው።
6從肉身生的就是肉身,從靈生的就是靈。
7ዳግመኛ ልትወለዱ ያስፈልጋችኋል ስላልሁህ አታድንቅ።
7你不要因為我對你說‘你們必須重生’而感到希奇。
8ነፋስ ወደሚወደው ይነፍሳል፥ ድምፁንም ትሰማለህ፥ ነገር ግን ከወዴት እንደ መጣ ወዴትም እንዲሄድ አታውቅም፤ ከመንፈስ የተወለደ ሁሉ እንዲሁ ነው።
8風隨意而吹,你聽見它的響聲,卻不知道它從哪裡來,往哪裡去;凡從聖靈生的,也是這樣。”
9ኒቆዲሞስ መልሶ። ይህ እንዴት ሊሆን ይችላል? አለው።
9尼哥德慕說:“怎能有這事呢?”
10ኢየሱስም መልሶ እንዲህ አለው። አንተ የእስራኤል መምህር ስትሆን ይህን አታውቅምን?
10耶穌說:“你是以色列人的教師,還不明白這事嗎?
11እውነት እውነት እልሃለሁ፥ የምናውቀውን እንናገራለን ያየነውንም እንመሰክራለን፥ ምስክራችንንም አትቀበሉትም።
11我實實在在告訴你,我們知道的,才講論;見過的,就作證,然而你們卻不接受我們的見證。
12ስለ ምድራዊ ነገር በነገርኋችሁ ጊዜ ካላመናችሁ፥ ስለ ሰማያዊ ነገር ብነግራችሁ እንዴት ታምናላችሁ?
12我對你們講地上的事,你們尚且不信,如果講天上的事,怎能相信呢?
13ከሰማይም ከወረደ በቀር ወደ ሰማይ የወጣ ማንም የለም፥ እርሱም በሰማይ የሚኖረው የሰው ልጅ ነው።
13除了那從天上降下來的人子(有些抄本作“除了那從天上降下來仍舊在天上的人子”),沒有人升過天。
14ሙሴም በምድረ በዳ እባብን እንደ ሰቀለ እንዲሁ በእርሱ የሚያምን ሁሉ የዘላለም ሕይወት እንዲኖረው እንጂ እንዳይጠፋ የሰው ልጅ ይሰቀል ይገባዋል።
14摩西在曠野怎樣把銅蛇舉起,人子也必照樣被舉起來,
16በእርሱ የሚያምን ሁሉ የዘላለም ሕይወት እንዲኖረው እንጂ እንዳይጠፋ እግዚአብሔር አንድያ ልጁን እስኪሰጥ ድረስ ዓለሙን እንዲሁ ወዶአልና።
15使所有信他的人都得永生。
17ዓለም በልጁ እንዲድን ነው እንጂ፥ በዓለም እንዲፈርድ እግዚአብሔር ወደ ዓለም አልላከውምና።
16“ 神愛世人,甚至把他的獨生子賜給他們,叫一切信他的,不至滅亡,反得永生。
18በእርሱ በሚያምን አይፈረድበትም፤ በማያምን ግን በአንዱ በእግዚአብሔር ልጅ ስም ስላላመነ አሁን ተፈርዶበታል።
17因為 神差他的兒子到世上來,不是要定世人的罪,而是要使世人藉著他得救。
19ብርሃንም ወደ ዓለም ስለ መጣ ሰዎችም ሥራቸው ክፉ ነበርና ከብርሃን ይልቅ ጨለማን ስለ ወደዱ ፍርዱ ይህ ነው።
18信他的,不被定罪;不信的,罪已經定了,因為他不信 神獨生子的名。
20ክፉ የሚያደርግ ሁሉ ብርሃንን ይጠላልና፥ ሥራውም እንዳይገለጥ ወደ ብርሃን አይመጣም፤
19光來到世上,世人因為自己的行為邪惡,不愛光倒愛黑暗,定他們罪的原因,就在這裡。
21እውነትን የሚያደርግ ግን ሥራው በእግዚአብሔር ተደርጎ እንደ ሆነ ይገለጥ ዘንድ ወደ ብርሃን ይመጣል።
20凡作惡的都恨光,不來接近光,免得他的惡行暴露出來。
22ከዚህ በኋላ ኢየሱስ ከደቀ መዛሙርቱ ጋር ወደ ይሁዳ አገር መጣ፥ በዚያም ከእነርሱ ጋር ተቀምጦ ያጠምቅ ነበር።
21凡行真理的,就來接近光,好顯明他所作的都是靠著 神而作的。”
23ዮሐንስም ደግሞ በሳሌም አቅራቢያ በሄኖን በዚያ ብዙ ውኃ ነበርና ያጠምቅ ነበር፥
22他必興旺,我必衰微這事以後,耶穌和門徒來到猶太地,他和他們住在那裡,並且施洗。
24እየመጡም ይጠመቁ ነበር ዮሐንስ ገና ወደ ወኅኒ አልተጨመረም ነበርና።
23約翰也在靠近撒冷的艾嫩施洗,因為那裡水多;眾人都去受洗。
25ስለዚህም በዮሐንስ ደቀ መዛሙርትና በአይሁድ መካከል ስለ ማንጻት ክርክር ሆነ።
24那時約翰還沒有入獄。
26ወደ ዮሐንስም መጥተው። መምህር ሆይ፥ በዮርዳኖስ ማዶ ከአንተ ጋር የነበረው አንተም የመሰከርህለት፥ እነሆ፥ እርሱ ያጠምቃል ሁሉም ወደ እርሱ ይመጣሉ አሉት።
25約翰的門徒和一個猶太人為潔淨禮發生辯論。
27ዮሐንስ መለሰ፥ እንዲህ ሲል። ከሰማይ ካልተሰጠው ሰው እንዳች ሊቀበል አይችልም።
26他們來到約翰那裡,對他說:“拉比,你看,從前和你在約旦河東,你為他作見證的那一位,他也在施洗,眾人都到他那裡去了。”
28እናንተ። እኔ ክርስቶስ አይደለሁም፥ ነገር ግን። ከእርሱ በፊት ተልኬአለሁ እንዳልሁ ራሳችሁ ትመሰክሩልኛላችሁ።
27約翰回答:“除了從天上賜下來給他的,人就不能得到甚麼。
29ሙሽራይቱ ያለችው እርሱ ሙሽራ ነው፤ ቆሞ የሚሰማው ሚዜው ግን በሙሽራው ድምጽ እጅግ ደስ ይለዋል። እንግዲህ ይህ ደስታዬ ተፈጸመ።
28你們自己可以為我作證:我曾說,我不是基督,不過是奉差遣作他的先鋒的。
30እርሱ ሊልቅ እኔ ግን ላንስ ያስፈልጋል።
29娶新娘的是新郎。新郎的好友站在那裡聽著,聽見新郎的聲音就非常喜樂。因此,我這喜樂滿溢了!
31ከላይ የሚመጣው ከሁሉ በላይ ነው፤ ከምድር የሚሆነው የምድር ነው የምድሩንም ይናገራል። ከሰማይ የሚመጣው ከሁሉ በላይ ነው።
30他必興旺,我必衰微。
32ያየውንና የሰማውንም ይህን ይመሰክራል፥ ምስክሩንም የሚቀበለው የለም።
31從天上來的“那從天上來的,是在萬有之上;從地上來的,是屬於地,所講的也是屬於地。那從天上來的,是超越萬有之上。
33ምስክሩን የተቀበለ እግዚአብሔር እውነተኛ እንደ ሆነ አተመ።
32他把所見所聞的見證出來,可是沒有人接受他的見證。
34እግዚአብሔር የላከው የእግዚአብሔርን ቃል ይናገራልና፤ እግዚአብሔር መንፈሱን ሰፍሮ አይሰጥምና።
33那接受他的見證的,就確認 神是真的。
35አባት ልጁን ይወዳል ሁሉንም በእጁ ሰጥቶታል።
34 神所差來的那一位講 神的話,因為 神把聖靈無限地賜給他。
36በልጁ የሚያምን የዘላለም ሕይወት አለው፤ በልጁ የማያምን ግን የእግዚአብሔር ቍጣ በእርሱ ላይ ይኖራል እንጂ ሕይወትን አያይም።
35父愛子,已經把萬有交在他手裡。
36信子的,有永生;不信從子的,必不得見永生, 神的震怒卻常在他身上。”