1ከዚህ በኋላ ኢየሱስ ወደ ገሊላ ባሕር ማዶ ተሻገረ፤ እርሱም የጥብርያዶስ ባሕር ነው።
1給五千人吃飽的神蹟(太14:13~21;可6:32~44;路9:10~17)這些事以後,耶穌渡過加利利海,就是提比里亞海。
2በበሽተኞችም ያደረገውን ምልክቶች ስላዩ ብዙ ሕዝብ ተከተሉት።
2有一大群人,因為看見了他在病人身上所行的神蹟,就跟隨了他。
3ኢየሱስም ወደ ተራራ ወጣና በዚያ ከደቀ መዛሙርቱ ጋር ተቀመጠ።
3耶穌上了山,同門徒坐在那裡。
4የአይሁድ በዓልም ፋሲካ ቀርቦ ነበር።
4那時猶太人的逾越節近了。
5ኢየሱስም ዓይኖቹን አንሥቶ ብዙ ሕዝብ ወደ እርሱ ሲመጣ አየና ፊልጶስን። እነዚህ እንዲበሉ እንጀራ ከወዴት እንገዛለን? አለው።
5耶穌舉目觀看,見一大群人向他走過來,就對腓力說:“我們從哪裡買餅給這些人吃呢?”
6ራሱ ሊያደርግ ያለውን ያውቅ ነበርና ሊፈትነው ይህን ተናገረ።
6他說這話,是要試驗腓力,因他自己早已知道要怎樣作。
7ፊልጶስ። እያንዳንዳቸው ትንሽ ትንሽ እንኳ እንዲቀበሉ የሁለት መቶ ዲናር እንጀራ አይበቃቸውም ብሎ መለሰለት።
7腓力回答:“就算二百銀幣買的餅,每人分一點,也是不夠的。”
8ከደቀ መዛሙርቱ አንዱ የስምዖን ጴጥሮስ ወንድም እንድርያስ።
8有一個門徒,就是西門.彼得的弟弟安得烈,對耶穌說:
9አምስት የገብስ እንጀራና ሁለት ዓሣ የያዘ ብላቴና በዚህ አለ፤ ነገር ግን እነዚህን ለሚያህሉ ሰዎች ይህ ምን ይሆናል? አለው።
9“這裡有個小孩子,帶著五個大麥餅、兩條魚;只是分給這麼多人,有甚麼用呢?”
10ኢየሱስም። ሰዎቹን እንዲቀመጡ አድርጉ አለ። በዚያም ስፍራ ብዙ ሣር ነበረበት። ወንዶችም ተቀመጡ ቍጥራቸውም አምስት ሺህ የሚያህል ነበር።
10耶穌吩咐他們:“你們叫眾人坐下。”原來那地方的草很多,眾人就坐下,單是男人的數目約有五千。
11ኢየሱስም እንጀራውን ያዘ፥ አመስግኖም ለደቀ መዛሙርቱ ሰጠ፥ ደቀ መዛሙርቱም ለተቀመጡት ሰዎች ሰጡአቸው እንዲሁም ከዓሣው በፈለጉት መጠን።
11耶穌拿起餅來,祝謝了,就分給坐著的人;分魚也是這樣,都是隨著他們所要的。
12ከጠገቡም በኋላ ደቀ መዛሙርቱን። አንድ ስንኳ እንዳይጠፋ የተረፈውን ቍርስራሽ አከማቹ አላቸው።
12他們吃飽了之後,耶穌對門徒說:“把剩下的零碎收拾起來,免得浪費。”
13ሰለዚህ አከማቹ፥ ከበሉትም ከአምስቱ የገብስ እንጀራ የተረፈውን ቍርስራሽ አሥራ ሁለት መሶብ ሞሉ።
13門徒就把眾人吃剩那五個大麥餅的零碎收拾起來,裝滿了十二個籃子。
14ከዚህ የተነሣ ሰዎቹ ኢየሱስ ያደረገውን ምልክት ባዩ ጊዜ። ይህ በእውነት ወደ ዓለም የሚመጣው ነቢይ ነው አሉ።
14眾人看見耶穌所行的神蹟,就說:“這真是那要到世上來的先知。”
15በዚህም ምክንያት ኢየሱስ ያነግሡት ዘንድ ሊመጡና ሊነጥቁት እንዳላቸው አውቆ ደግሞ ወደ ተራራ ብቻውን ፈቀቅ አለ።
15耶穌知道群眾要來強迫他作王,就獨自又退到山上去了。
16በመሸም ጊዜ ደቀ መዛሙርቱ ወደ ባሕር ወረዱ፥
16耶穌在海面上行走(太14:22~33;可6:47~51)到了晚上,他的門徒下到海邊去。
17በታንኳም ገብተው በባሕር ማዶ ወደ ቅፍርናሆም ይመጡ ነበር። አሁንም ጨልሞ ነበር፤ ኢየሱስም ገና ወደ እነርሱ አልመጣም ነበር፤
17他們上了船,要渡海往迦百農去。那時天已經黑了,耶穌還沒有到他們那裡。
18ብርቱ ነፋስም ስለ ነፈሰ ባሕሩ ተናወጠ።
18忽然海上起了狂風,波浪翻騰。
19ሀያ አምስት ወይም ሠላሳ ምዕራፍ ከቀዘፉ በኋላም፥ ኢየሱስ በባሕር ላይ እየሄደ ወደ ታንኳይቱ ሲቀርብ አይተው ፈሩ።
19門徒搖櫓約行了五六公里,看見耶穌在海面上行走,漸漸靠近船,就害怕起來。
20እርሱ ግን። እኔ ነኝ፤ አትፍሩ አላቸው።
20耶穌對他們說:“是我,不要怕。”
21ስለዚህ በታንኳይቱ ሊቀበሉት ወደዱ፤ ወዲያውም ታንኳይቱ ወደሚሄዱበት ምድር ደረሰች።
21他們這才把他接上船,船就立刻到了他們要去的地方。
22በነገው በባሕር ማዶ ቆመው የነበሩ ሕዝቡ ከአንዲት ጀልባ በቀር በዚያ ሌላ ጀልባ እንዳልነበረች፥ ደቀ መዛሙርቱም ለብቻቸው እንደ ሄዱ እንጂ ኢየሱስ ከደቀ መዛሙርቱ ጋር ወደ ታንኳይቱ እንዳልገባ አዩ፤
22耶穌是生命的食物第二天,站在海那邊的群眾,看見只有一隻小船留在那裡,並且知道耶穌沒有和他的門徒一同上船,門徒是自己去的;
23ዳሩ ግን ሌሎች ጀልባዎች ጌታ የባረከውን እንጀራ ወደ በሉበት ስፍራ አጠገብ ከጥብርያዶስ መጡ።
23不過有幾隻從提比里亞來的船停在那裡,靠近他們在主祝謝以後吃餅的地方。
24ሕዝቡም ኢየሱስ ወይም ደቀ መዛሙርቱ በዚያ እንዳልነበሩ ባዩ ጊዜ፥ ራሳቸው በጀልባዎቹ ገብተው ኢየሱስን እየፈለጉ ወደ ቅፍርናሆም መጡ።
24群眾見耶穌和門徒都不在那裡,就上船往迦百農去找耶穌。
25በባሕር ማዶም ሲያገኙት። መምህር ሆይ፥ ወደዚህ መቼ መጣህ? አሉት።
25他們在對岸找到了耶穌,就問他:“拉比,你幾時到這裡來的?”
26ኢየሱስም መልሶ። እውነት እውነት እላችኋለሁ፥ የምትፈልጉኝ እንጀራን ስለ በላችሁና ስለ ጠገባችሁ ነው እንጂ ምልክቶችን ስላያችሁ አይደለም።
26耶穌回答:“我實實在在告訴你們,你們找我,不是因為看見了神蹟,而是因為吃了餅又吃飽了。
27ለሚጠፋ መብል አትሥሩ፤ ነገር ግን ለዘላለም ሕይወት ለሚኖር መብል የሰው ልጅ ለሚሰጣችሁ ሥሩ፤ እርሱን እግዚአብሔር አብ አትሞታልና።
27不要為那必朽壞的食物操勞,卻要為那存到永生的食物操勞,就是人子所要賜給你們的,因為人子是父 神所印證的。”
28እንግዲህ። የእግዚአብሔርን ሥራ እንድንሠራ ምን እናድርግ? አሉት።
28眾人又問他:“我們應該作甚麼,才算是作 神的工作呢?”
29ኢየሱስ መልሶ። ይህ የእግዚአብሔር ሥራ እርሱ በላከው እንድታምኑ ነው አላቸው።
29耶穌回答:“信 神所差來的,就是作 神的工了。”
30እንግዲህ። እንኪያ አይተን እንድናምንህ አንተ ምን ምልክት ታደርጋለህ? ምንስ ትሠራለህ?
30於是他們就說:“你要行甚麼神蹟,讓我們看了就信你呢?你到底能作甚麼呢?
31ይበሉ ዘንድ ከሰማይ እንጀራ ሰጣቸው ተብሎ እንደ ተጻፈ አባቶቻችን በምድረ በዳ መና በሉ አሉት።
31我們的祖宗在曠野吃過嗎哪,正如經上所記:‘他把從天上來的食物賜給他們吃。’”
32ኢየሱስም። እውነት እውነት እላችኋለሁ፥ እውነተኛ እንጀራ ከሰማይ የሚሰጣችሁ አባቴ ነው እንጂ ከሰማይ እንጀራ የሰጣችሁ ሙሴ አይደለም፤
32耶穌對他們說:“我實實在在告訴你們,不是摩西把那從天上來的食物賜給你們,而是我父把天上來的真食物賜給你們;
33የእግዚአብሔር እንጀራ ከሰማይ የሚወርድ ለዓለምም ሕይወትን የሚሰጥ ነውና አላቸው።
33因為 神的食物就是從天上降下來,把生命賜給世人的那一位。”
34ስለዚህ። ጌታ ሆይ፥ ይህን እንጀራ ዘወትር ስጠን አሉት።
34他們對耶穌說:“主啊,求你常把這食物賜給我們。”
35ኢየሱስም እንዲህ አላቸው። የሕይወት እንጀራ እኔ ነኝ፤ ወደ እኔ የሚመጣ ከቶ አይራብም በእኔ የሚያምንም ሁልጊዜ ከቶ አይጠማም።
35耶穌說:“我就是生命的食物,到我這裡來的,必定不餓;信我的,永遠不渴。
36ነገር ግን አይታችሁኝ እንዳላመናችሁ አልኋችሁ።
36但我告訴你們,你們雖然見了我,還是不信。
37አብ የሚሰጠኝ ሁሉ ወደ እኔ ይመጣል፥ ወደ እኔም የሚመጣውን ከቶ ወደ ውጭ አላወጣውም፤
37凡是父賜給我的人,必到我這裡來;到我這裡來的,我決不丟棄他,
38ፈቃዴን ለማድረግ አይደለም እንጂ የላከኝን ፈቃድ ለማድረግ ከሰማይ ወርጃለሁና።
38因為我從天上降下來,不是要行自己的意思,而是要行那差我來者的旨意。
39ከሰጠኝም ሁሉ አንድን ስንኳ እንዳላጠፋ በመጨረሻው ቀን እንዳስነሣው እንጂ የላከኝ የአብ ፈቃድ ይህ ነው።
39那差我來者的旨意就是:他所賜給我的人,我連一個也不失落,並且在末日我要使他們復活。
40ልጅንም አይቶ በእርሱ የሚያምን ሁሉ የዘላለም ሕይወትን እንዲያገኝ የአባቴ ፈቃድ ይህ ነው፥ እኔም በመጨረሻው ቀን አስነሣዋለሁ።
40因為我父的旨意,是要使所有看見了子而信的人有永生,並且在末日我要使他們復活。”
41እንግዲህ አይሁድ። ከሰማይ የወረደ እንጀራ እኔ ነኝ ስላለ ስለ እርሱ አንጐራጐሩና።
41猶太人因為耶穌說“我是從天上降下來的食物”,就紛紛議論他。
42አባቱንና እናቱን የምናውቃቸው ይህ የዮሴፍ ልጅ ኢየሱስ አይደለምን? እንግዲህ። ከሰማይ ወርጃለሁ እንዴት ይላል? አሉ።
42他們說:“這不是約瑟的兒子耶穌嗎?他的父母我們不都認識嗎?他現在怎麼說‘我是從天上降下來的’呢?”
43ኢየሱስ መለሰ አላቸውም። እርስ በርሳችሁ አታንጐራጕሩ።
43耶穌回答:“你們不要彼此議論。
44የላከኝ አብ ከሳበው በቀር ወደ እኔ ሊመጣ የሚችል የለም፥ እኔም በመጨረሻው ቀን አስነሣዋለሁ።
44如果不是差我來的父吸引人,就沒有人能到我這裡來;到我這裡來的,在末日我要使他復活。
45ሁሉም ከእግዚአብሔር የተማሩ ይሆናሉ ተብሎ በነቢያት ተጽፎአል፤ እንግዲህ ከአብ የሰማ የተማረም ሁሉ ወደ እኔ ይመጣል።
45先知書上記著:‘眾人都必受 神的教導。’凡聽見從父那裡來的教訓而又學習的,必到我這裡來。
46አብን ያየ ማንም የለም፤ ከእግዚአብሔር ከሆነ በቀር፥ እርሱ አብን አይቶአል።
46這不是說有人見過父;只有從 神那裡來的那一位,他才見過父。
47እውነት እውነት እላችኋለሁ በእኔ የሚያምን የዘላለም ሕይወት አለው።
47我實實在在告訴你們,信的人有永生。
48የሕይወት እንጀራ እኔ ነኝ።
48我就是生命的食物,
49አባቶቻችሁ በምድረ በዳ መና በሉ ሞቱም፤
49你們的祖宗在曠野吃過嗎哪,還是死了。
50ሰው ከእርሱ በልቶ እንዳይሞት ከሰማይ አሁን የወረደ እንጀራ ይህ ነው።
50這是從天上降下來的食物,使人吃了就不死。
51ከሰማይ የወረደ ሕያው እንጀራ እኔ ነኝ፤ ሰው ከዚህ እንጀራ ቢበላ ለዘላለም ይኖራል፤ እኔም ስለ ዓለም ሕይወት የምሰጠው እንጀራ ሥጋዬ ነው።
51我就是從天上降下來生命的食物,人若吃了這食物,就必活到永遠。我要賜的食物就是我的肉,是為了世人的生命而賜的。”
52እንግዲህ አይሁድ። ይህ ሰው ሥጋውን ልንበላ ይሰጠን ዘንድ እንዴት ይችላል? ብለው እርስ በርሳቸው ተከራከሩ።
52於是,猶太人彼此爭論,說:“這個人怎能把他的肉給我們吃呢?”
53ስለዚህ ኢየሱስ እንዲህ አላቸው። እውነት እውነት እላችኋለሁ፥ የሰውን ልጅ ሥጋ ካልበላችሁ ደሙንም ካልጠጣችሁ በራሳችሁ ሕይወት የላችሁም።
53耶穌就對他們說:“我實實在在告訴你們,你們若不吃人子的肉,不喝人子的血,就沒有生命在你們裡面。
54ሥጋዬን የሚበላ ደሜንም የሚጠጣ የዘላለም ሕይወት አለው፥ እኔም በመጨረሻው ቀን አስነሣዋለሁ።
54吃我肉、喝我血的,就有永生,在末日我要使他復活;
55ሥጋዬ እውነተኛ መብል ደሜም እውነተኛ መጠጥ ነውና።
55因為我的肉是真正的食物,我的血是真正的飲料。
56ሥጋዬን የሚበላ ደሜንም የሚጠጣ በእኔ ይኖራል እኔም በእርሱ እኖራለሁ።
56吃我肉、喝我血的人,就住在我裡面,我也住在他裡面。
57ሕያው አብ እንደ ላከኝ እኔም ከአብ የተነሣ ሕያው እንደምሆን፥ እንዲሁ የሚበላኝ ደግሞ ከእኔ የተነሣ ሕያው ይሆናል።
57正如永活的父差遣了我,我也因父活著;照樣,吃我肉的人也必因我而活。
58ከሰማይ የወረደ እንጀራ ይህ ነው፤ አባቶቻችሁ መና በልተው እንደ ሞቱ አይደለም፤ ይህን እንጀራ የሚበላ ለዘላለም ይኖራል
58這就是從天上降下來的食物,不像嗎哪,你們的祖宗吃過,還是死了;吃這食物的,必活到永遠。”
59በቅፍርናሆም ሲያስተምር ይህን በምኵራብ አለ።
59這些話是耶穌在迦百農會堂裡教導人的時候說的。
60ከደቀ መዛሙርቱም ብዙዎች በሰሙ ጊዜ። ይህ የሚያስጨንቅ ንግግር ነው፤ ማን ሊሰማው ይችላል? አሉ።
60永生之道他的門徒中,有許多人聽了,就說:“這話很難,誰能接受呢?”
61ኢየሱስ ግን ደቀ መዛሙርቱ ስለዚህ እንዳንጐራጐሩ በልቡ አውቆ አላቸው። ይህ ያሰናክላችኋልን?
61耶穌心裡知道門徒為了這事議論紛紛,就對他們說:“這話使你們動搖嗎?
62እንግዲህ የሰው ልጅ አስቀድሞ ወደ ነበረበት ሲወጣ ብታዩ እንዴት ይሆናል?
62如果你們看見人子升到他原來所在的地方,又怎樣呢?
63ሕይወትን የሚሰጥ መንፈስ ነው፤ ሥጋ ምንም አይጠቅምም፤ እኔ የነገርኋችሁ ቃል መንፈስ ነው ሕይወትም ነው።
63使人活的是靈,肉體是無濟於事的。我對你們所說的話是靈、是生命。
64ነገር ግን ከእናንተ የማያምኑ አሉ። ኢየሱስ የማያምኑት እነማን እንደ ሆኑ አሳልፎ የሚሰጠውም ማን እንደ ሆነ ከመጀመሪያ ያውቅ ነበርና።
64然而你們中間卻有不信的人。”原來從起初耶穌就知道那些不信的是誰,那要把他出賣的又是誰。
65ደግሞ። ስለዚህ አልኋችሁ፥ ከአብ የተሰጠው ካልሆነ ወደ እኔ ሊመጣ የሚችል የለም አለ።
65耶穌跟著說:“所以我對你們說過,如果不是父所賜的,沒有人能到我這裡來。”
66ከዚህም የተነሣ ከደቀ መዛሙርቱ ብዙዎች ወደ ኋላ ተመለሱ፤ ወደ ፊትም ከእርሱ ጋር አልሄዱም።
66從此,他的門徒中有許多人退去了,不再與他同行。
67ኢየሱስም ለአሥራ ሁለቱ። እናንተ ደግሞ ልትሄዱ ትወዳላችሁን? አለ።
67於是耶穌對十二門徒說:“你們也想離去嗎?”
68ስምዖን ጴጥሮስ። ጌታ ሆይ፥ ወደ ማን እንሄዳለን? አንተ የዘላለም ሕይወት ቃል አለህ፤
68西門.彼得回答:“主啊,你有永生之道,我們還跟從誰呢?
69እኛስ አንተ ክርስቶስ የሕያው የእግዚአብሔር ልጅ እንደ ሆንህ አምነናል አውቀናልም ብሎ መለሰለት።
69我們已經相信,並且知道你是 神的聖者。”
70ኢየሱስም። እኔ እናንተን አሥራ ሁለታችሁን የመረጥኋችሁ አይደለምን? ከእናንተም አንዱ ዲያብሎስ ነው ብሎ መለሰላቸው።
70耶穌說:“我不是揀選了你們十二個人嗎?但你們中間有一個是魔鬼。”
71ስለ ስምዖንም ልጅ ስለ አስቆሮቱ ይሁዳ ተናገረ፤ ከአሥራ ሁለቱ አንዱ የሆነ እርሱ አሳልፎ ይሰጠው ዘንድ አለውና።
71耶穌這話是指著加略人西門的兒子猶大說的,因為他雖然是十二門徒之一,卻要出賣耶穌。