1ወደ ባሕር ማዶም ወደ ጌርጌሴኖን አገር መጡ።
1治好鬼附的格拉森人(太8:28~34;路8:26~39)他們到了海的那邊,進入格拉森人的地區。
2ከታንኳይቱም በወጣ ጊዜ፥ ርኵስ መንፈስ የያዘው ሰው ከመቃብር ወጥቶ ወዲያው ተገናኘው፤
2耶穌一下船,就有一個被污靈附著的人,從墓地裡迎面而來。
3እርሱም በመቃብር ይኖር ነበር፥ በሰንሰለትም ስንኳ ማንም ሊያስረው በዚያን ጊዜ አይችልም ነበር፤
3那人經常住在墳墓中間,從來沒有人能綁住他,甚至用鎖鍊都不能。
4ብዙ ጊዜ በእግር ብረትና በሰንሰለት ይታሰር ነበርና ዳሩ ግን ሰንሰለቱን ይበጣጥስ እግር ብረቱንም ይሰባብር ነበር፥ ሊያሸንፈውም የሚችል አልነበረም፤
4曾經有很多次,人用腳鐐和鎖鍊捆綁他,鎖鍊卻被他掙斷,腳鐐也被他弄碎,始終沒有人能制伏他。
5ሁልጊዜም ሌሊትና ቀን በመቃብርና በተራራ ሆኖ ይጮኽ ነበር ሰውነቱንም በድንጋይ ይቧጭር ነበር።
5他晝夜在墳墓裡和山野間喊叫,又用石頭砍自己。
6ኢየሱስንም ከሩቅ ባየ ጊዜ ሮጦ ሰገደለት፥
6他遠遠地看見耶穌,就跑過去拜他,
7በታላቅ ድምፅም እየጮኸ። የልዑል እግዚአብሔር ልጅ ኢየሱስ ሆይ፥ ከአንተ ጋር ምን አለኝ? እንዳታሠቃየኝ በእግዚአብሔር አምልሃለሁ አለ፤
7大聲呼叫,說:“至高 神的兒子耶穌,我跟你有甚麼關係呢?我指著 神懇求你,不要叫我受苦。”
8አንተ ርኵስ መንፈስ፥ ከዚህ ሰው ውጣ ብሎት ነበርና።
8因為當時耶穌吩咐他:“你這污靈,從這人身上出來!”
9ስምህ ማን ነው? ብሎ ጠየቀው። ብዙዎች ነንና ስሜ ሌጌዎን ነው አለው፥
9耶穌問他:“你叫甚麼名字?”他回答:“我名叫‘群’,因為我們眾多。”
10ከአገርም ውጭ እንዳይሰዳቸው አጥብቆ ለመነው።
10他再三央求耶穌,不要把他們從那地方趕走。
11በዚያም በተራራ ጥግ ብዙ የእሪያ መንጋ ይሰማራ ነበርና።
11附近的山坡上有一大群豬正在吃東西;
12ወደ እሪያዎቹ እንድንገባ ስደደን ብለው ለመኑት።
12污靈求耶穌說:“打發我們到豬群那裡附在豬身上吧。”
13ኢየሱስም ፈቀደላቸው። ርኵሳን መናፍስቱም ወጥተው ወደ እሪያዎቹ ገቡ፥ ሁለት ሺህም የሚያህል መንጋ ከአፋፉ ወደ ባሕር ተጣደፉና በባሕር ሰጠሙ።
13耶穌准了他們。污靈就出來,進到豬群裡去,於是那群豬闖下山崖,掉在海裡淹死了,豬的數目約有兩千。
14እረኞቹም ሸሽተው በከተማውና በአገሩ አወሩ፤ ነገሩም ምን እንደ ሆነ ለማየት መጡ።
14放豬的人都逃跑了,到城裡和各鄉村去報告,大家就來看發生了甚麼事。
15ወደ ኢየሱስም መጡ፥ አጋንንትም ያደሩበትን ሌጌዎንም የነበረበትን ሰው ተቀምጦ ለብሶም ልቡም ተመልሶ አዩና ፈሩ።
15他們來到耶穌跟前,看見那被鬼附過的人,就是曾被名叫‘群’的鬼附過的人,坐在那裡,穿上了衣服,神志清醒,他們就害怕。
16ያዩት ሰዎችም አጋንንት ላደሩበት ሰው የሆነውንና ስለ እሪያዎቹ ተረኩላቸው።
16看見的人把被鬼附過的人所遭遇的和那群豬的事,告訴了他們。
17ከአገራቸውም እንዲሄድላቸው ይለምኑት ጀመር።
17他們就要求耶穌離開他們的地區。
18ወደ ታንኳይቱም በገባ ጊዜ አጋንንት አድረውበት የነበረው ሰው ከእርሱ ጋር እንዲኖር ለመነው።
18耶穌上船的時候,那被鬼附過的人來求他,要和他在一起。
19ኢየሱስም አልፈቀደለትም፥ ነገር ግን። ወደ ቤትህ በቤተ ሰዎችህ ዘንድ ሄደህ ጌታ እንዴት ያለ ታላቅ ነገር እንዳደረገልህ እንዴትስ እንደ ማረህ አውራላቸው አለው።
19耶穌不許,卻對他說:“你回家到你的親屬那裡去,把主為你作了多麼大的事,並他怎樣憐憫你,都告訴他們。”
20ሄዶም ኢየሱስ እንዴት ያለ ታላቅ ነገር እንዳደረገለት አሥር ከተማ በሚባል አገር ይሰብክ ጀመር፥ ሁሉም ተደነቁ።
20那人就走了,開始在低加波利傳講耶穌為他所作的大事,眾人都希奇。
21ኢየሱስም ደግሞ በታንኳይቱ ወደ ማዶ ከተሻገረ በኋላ ብዙ ሰዎች ወደ እርሱ ተሰበሰቡ፥ በባሕርም አጠገብ ነበረ።
21治好血漏病的女人(太9:18~26;路8:40~56)耶穌又坐船渡到那邊;還在海邊的時候,有一大群人向他圍攏過來。
22ኢያኢሮስ የተባለ ከምኵራብ አለቆች አንዱ መጣ፤ ባየውም ጊዜ በእግሩ ላይ ወደቀና።
22當時來了一位會堂的主管,名叫葉魯。他一看見耶穌,就俯伏在他腳前,
23ታናሽቱ ልጄ ልትሞት ቀርባለችና እንድትድንና በሕይወት እንድትኖር መጥተህ እጅህን ጫንባት ብሎ አጥብቆ ለመነው።
23迫切地求他說:“我的小女兒快要死了,請你來按手在她身上,把她救活。”
24ከእርሱም ጋር ሄደ። ብዙ ሕዝብም ተከተሉት አጋፉትም።
24耶穌就和他一起去了。一大群人跟著他,擁擠著他。
25ከአሥራ ሁለት ዓመትም ጀምሮ ደም የሚፈሳት ሴት ነበረች፥
25有一個女人,患了十二年的血漏病,
26ከብዙ ባለ መድኃኒቶችም ብዙ ተሠቃየች፤ ገንዘብዋንም ሁሉ ከስራ ባሰባት እንጂ ምንም አልተጠቀመችም፤
26在好些醫生手中受了許多痛苦,又花盡了她一切所有的,不僅毫無起色,反而更加沉重。
27የኢየሱስንም ወሬ ሰምታ በስተኋላው በሰዎች መካከል መጥታ ልብሱን ዳሰሰች።
27她聽見耶穌的事,就從後面來雜在人群中間,摸耶穌的衣服。
28ልብሱን ብቻ የዳሰስሁ እንደ ሆነ እድናለሁ ብላለችና።
28因為她說:“只要摸到他的衣服,我就必痊愈。”
29ወዲያውም የደምዋ ምንጭ ደረቀ ከሥቃይዋም እንደዳነች በሰውነትዋ አወቀች።
29於是她血漏的源頭立刻乾了,她在身體上感覺到病已經得了醫治。
30ወዲያውም ኢየሱስ ከእርሱ ኃይል እንደ ወጣ በገዛ ራሱ አውቆ በሕዝቡ መካከል ዘወር ብሎ። ልብሴን የዳሰሰ ማን ነው? አለ።
30耶穌自己立刻覺得有能力從他裡面出去,就轉過身來對群眾說:“誰摸了我的衣服?”
31ደቀ መዛሙርቱም። ሕዝቡ ሲያጋፉህ እያየህ። ማን ዳሰሰኝ ትላለህን? አሉት።
31門徒對他說:“你看,這麼多人擁擠你,你還問‘誰摸我’嗎?”
32ይህንም ያደረገችውን ለማየት ዘወር ብሎ ይመለከት ነበር።
32耶穌周圍觀看,要看作這事的女人。
33ሴቲቱ ግን የተደረገላትን ስላወቀች፥ እየፈራች እየተንቀጠቀጠችም፥ መጥታ በፊቱ ተደፋች እውነቱንም ሁሉ ነገረችው።
33那女人知道在她身上所成就的事,就恐懼戰兢地前來向耶穌俯伏,把實情全告訴了他。
34እርሱም። ልጄ ሆይ፥ እምነትሽ አድኖሻል፤ በሰላም ሂጂ ከሥቃይሽም ተፈወሽ አላት።
34耶穌對她說:“女兒,你的信使你痊愈了,平安地回去吧,你的病已經好了。”
35እርሱም ገና ሲናገር ከምኵራብ አለቃው ቤት ዘንድ የመጡት። ልጅህ ሞታለች፤ ስለ ምን መምህሩን አሁን ታደክመዋለህ? አሉት።
35使女孩復活耶穌還在說話的時候,有人從會堂主管的家裡來說:“你的女兒已經死了,何必還勞動老師呢?”
36ኢየሱስ ግን የተናገሩትን ቃል አድምጦ ለምኵራቡ አለቃ። እመን ብቻ እንጂ አትፍራ አለው።
36耶穌聽見所說的話,就對會堂主管說:“不要怕!只要信!”
37ከጴጥሮስም ከያዕቆብም ከያዕቆብም ወንድም ከዮሐንስ በቀር ማንም እንዲከተለው አልፈቀደም።
37於是他不許別人跟他一起去,只帶了彼得、雅各和雅各的弟弟約翰。
38ወደ ምኵራቡ አለቃ ቤትም መጥቶ ሰዎች ሲንጫጩና ሲያለቅሱ ዋይታም ሲያበዙ አየ፤
38他們來到會堂主管的家,耶穌看見許多人哭泣哀號,一片混亂,
39ገብቶም። ስለ ምን ትንጫጫላችሁ ታለቅሳላችሁም? ብላቴናይቱ ተኝታለች እንጂ አልሞተችም አላቸው።
39就走進去,對眾人說:“為甚麼大哭大嚷呢?孩子不是死了,是睡著了。”
40በጣምም ሳቁበት። እርሱ ግን ሁሉን አስወጥቶ የብላቴናይቱን አባትና እናትም ከእርሱ ጋር የነበሩትንም ይዞ ብላቴናይቱ ወዳለችበት ገባ።
40眾人就嘲笑他。耶穌把眾人都趕出去,帶著孩子的父母和跟隨他的門徒,進入孩子所在的房間。
41የብላቴናይቱንም እጅ ይዞ። ጣሊታ ቁሚ አላት፤ ፍችውም አንቺ ብላቴና ተነሽ እልሻለሁ ነው።
41耶穌拉著孩子的手,對她說:“大利大,古米!”翻譯出來就是:“小女孩,我吩咐你起來!”
42ብላቴናይቱም የአሥራ ሁለት ዓመት ልጅ ነበረችና ወዲያው ቆማ ተመላለሰች። ወዲያውም ታላቅ መገረም ተገረሙ።
42那女孩子就立刻起來行走;那時她已經十二歲了。眾人就非常驚奇。
43ይህንም ማንም እንዳያውቅ አጥብቆ አዞአቸው። የምትበላውን ስጡአት አላቸው።
43耶穌再三囑咐他們,不要讓人知道這事,又吩咐給她東西吃。