Amharic: New Testament

聖經新譯本

Matthew

17

1ከስድስት ቀንም በኋላ ኢየሱስ ጴጥሮስንና ያዕቆብን ወንድሙንም ዮሐንስን ይዞ ወደ ረጅም ተራራ ብቻቸውን አወጣቸው።
1在山上改變形象(可9:2~13;路9:28~36)過了六天,耶穌帶著彼得、雅各和雅各的弟弟約翰,領他們悄悄地上了高山。
2በፊታቸውም ተለወጠ፥ ፊቱም እንደ ፀሐይ በራ፥ ልብሱም እንደ ብርሃን ነጭ ሆነ።
2耶穌在他們面前改變了形象,臉好像太陽一樣照耀,衣服潔白像光。
3እነሆም፥ ሙሴና ኤልያስ ከእርሱ ጋር ሲነጋገሩ ታዩአቸው።
3忽然,摩西和以利亞向他們顯現,跟耶穌談話。
4ጴጥሮስም መልሶ ኢየሱስን። ጌታ ሆይ፥ በዚህ መሆን ለእኛ መልካም ነው፤ ብትወድስ፥ በዚህ ሦስት ዳስ አንዱን ለአንተ አንዱንም ለሙሴ አንዱንም ለኤልያስ እንሥራ አለ።
4彼得對耶穌說:“主啊,我們在這裡真好。如果你願意,我就在這裡搭三個帳棚,一個為你,一個為摩西,一個為以利亞。”
5እርሱም ገና ሲናገር፥ እነሆ፥ ብሩህ ደመና ጋረዳቸው፥ እነሆም፥ ከደመናው። በእርሱ ደስ የሚለኝ የምወደው ልጄ ይህ ነው፤ እርሱን ስሙት የሚል ድምፅ መጣ።
5彼得還說話的時候,有一朵明亮的雲彩籠罩他們,雲中有聲音說:“這是我的愛子,我所喜悅的,你們要聽他。”
6ደቀ መዛሙርቱም ሰምተው በፊታቸው ወደቁ እጅግም ፈርተው ነበር።
6門徒聽見了,就俯伏在地上,非常害怕。
7ኢየሱስም ቀርቦ ዳሰሳቸውና። ተነሡ አትፍሩም አላቸው።
7耶穌前來,摸著他們說:“起來,不用怕。”
8ዓይናቸውንም አቅንተው ሲያዩ ከኢየሱስ ብቻ በቀር ማንንም አላዩም።
8他們抬起頭來,看見只有耶穌自己,沒有別的人。
9ከተራራውም በወረዱ ጊዜ ኢየሱስ። የሰው ልጅ ከሙታን እስኪነሣ ድረስ ያያችሁትን ለማንም አትንገሩ ብሎ አዘዛቸው።
9他們下山的時候,耶穌吩咐他們:“人子從死人中復活以前,你們不要把所看見的異象告訴人。”
10ደቀ መዛሙርቱም። እንግዲህ ጻፎች። ኤልያስ አስቀድሞ ሊመጣ ይገባዋል ስለ ምን ይላሉ? ብለው ጠየቁት።
10門徒就問他:“那麼經學家為甚麼說,以利亞必須先來呢?”
11ኢየሱስም መልሶ። ኤልያስማ አስቀድሞ ይመጣል ሁሉንም ያቀናል፤
11他回答:“以利亞當然要來,並且復興一切。
12ነገር ግን እላችኋለሁ፥ ኤልያስ ከዚህ በፊት መጣ፤ የወደዱትንም ሁሉ አደረጉበት እንጂ አላወቁትም፤ እንዲሁም ደግሞ የሰው ልጅ ከእነርሱ መከራ ይቀበል ዘንድ አለው አላቸው።
12但我告訴你們,以利亞已經來了,可是人們卻不認識他,反而任意待他。照樣,人子也要這樣被他們苦待。”
13በዚያን ጊዜ ደቀ መዛሙርቱ ስለ መጥምቁ ስለ ዮሐንስ እንደ ነገራቸው አስተዋሉ።
13這時門徒才領悟,耶穌是指著施洗的約翰說的。
14ወደ ሕዝቡም ሲደርሱ አንድ ሰው ወደ እርሱ ቀረበና ተንበርክኮ። ጌታ ሆይ፥ ልጄን ማርልኝ፥ በጨረቃ እየተነሣበት ክፉኛ ይሣቀያልና፤
14治好癲癇病的小孩(可9:14~29;路9:37~42)耶穌和門徒來到群眾那裡,有一個人前來,跪下對耶穌說:
15ብዙ ጊዜ በእሳት ብዙ ጊዜም በውኃ ይወድቃልና።
15“主啊,可憐我的兒子吧,他患了癲癇病,非常痛苦,好幾次掉進火裡和水中。
16ወደ ደቀ መዛሙርትህም አመጣሁት ሊፈውሱትም አቃታቸው አለው።
16我帶他去見你的門徒,他們卻不能醫好他。”
17ኢየሱስም መልሶ። የማታምን ጠማማ ትውልድ ሆይ፥ እስከ መቼ ከእናንተ ጋር እኖራለሁ? እስከ መቼስ እታገሣችኋለሁ? ወደዚህ ወደ እኔ አምጡት አለ።
17耶穌說:“唉!這又不信又乖謬的世代啊!我要跟你們在一起到幾時呢?我要忍受你們到幾時呢?把孩子帶到我這裡來吧。”
18ኢየሱስም ገሠጸው ጋኔኑም ከእርሱ ወጣ፥ ብላቴናውም ከዚያች ሰዓት ጀምሮ ተፈወሰ።
18耶穌斥責那鬼,鬼就從孩子身上出來;從那時起,孩子就好了。
19ከዚህ በኋላ ደቀ መዛሙርቱ ብቻቸውን ወደ ኢየሱስ ቀረቡና። እኛ ልናወጣው ያልቻልን ስለ ምን ነው? አሉት።
19門徒悄悄地前來問耶穌:“為甚麼我們不能把鬼趕出去呢?”
20ኢየሱስም። ስለ እምነታችሁ ማነስ ነው፤ እውነት እላችኋለሁ፥ የሰናፍጭ ቅንጣት የሚያህል እምነት ቢኖራችሁ፥ ይህን ተራራ። ከዚህ ወደዚያ እለፍ ብትሉት ያልፋል፤ የሚሳናችሁም ነገር የለም።
20他說:“因為你們的信心太小了。我實在告訴你們,只要你們的信心像一粒芥菜種,就是對這山說:‘從這裡移到那裡’,它也必移開。沒有甚麼是你們不能作的。”
21ይህ ዓይነት ግን ከጸሎትና ከጦም በቀር አይወጣም አላቸው።
21(有些抄本有第21節:“這一類的鬼,如果不靠禱告和禁食,是趕不出來的。”)
22በገሊላም ሲመላለሱ ኢየሱስ። የሰው ልጅ በሰዎች እጅ አልፎ ይሰጥ ዘንድ አለው፥ ይገድሉትማል፥
22第二次預言受難及復活(可9:30~32;路9:43~45)他們聚集在加利利的時候,耶穌對門徒說:“人子將要被交在人的手裡,
23በሦስተኛውም ቀን ይነሣል አላቸው። እጅግም አዘኑ።
23他們要殺害他,第三天他要復活。”他們就很憂愁。
24ወደ ቅፍርናሆምም በመጡ ጊዜ ግብር የሚቀበሉ ሰዎች ወደ ጴጥሮስ ቀረቡና። መምህራችሁ ሁለቱን ዲናር*ፍ1* አይገብርምን? አሉት።
24繳納殿稅他們來到迦百農,收殿稅的人前來對彼得說:“你們的老師不納稅嗎?”
25አዎን ይገብራል አለ። ወደ ቤትም በገባ ጊዜ ኢየሱስ አስቀድሞ። ስምዖን ሆይ፥ ምን ይመስልሃል? የምድር ነገሥታት ቀረጥና ግብር ከማን ይቀበላሉ? ከልጆቻቸውን ወይስ ከእንግዶች? አለው።
25他說:“納。”他進到屋子裡,耶穌先問他:“西門,你認為怎樣?地上的君王向誰徵收關稅和丁稅?向自己的兒子還是外人呢?”
26ጴጥሮስም። ከእንግዶች ባለው ጊዜ ኢየሱስ። እንኪያስ ልጆቻቸው ነጻ ናቸው።
26他回答:“外人。”耶穌對他說:“這樣,兒子就可以免稅了。
27ነገር ግን እንዳናሰናክላቸው፥ ወደ ባሕር ሂድና መቃጥን ጣል፥ መጀመሪያም የሚወጣውን ዓሣ ውሰድና አፉን ስትከፍት እስታቴር*ፍ2* ታገኛለህ፤ ያን ወስደህ ስለ እኔና ስለ አንተ ስጣቸው አለው።
27但為了避免觸犯他們,你要到海邊去釣魚;把第一條釣上來的魚拿起來,打開魚的嘴,你就會找到一個大銀幣。你可以拿去交給他們作你我的殿稅。”