1ኢየሱስም መለሰ ደግሞም በምሳሌ ነገራቸው እንዲህም አለ።
1婚筵的比喻(路14:16~24)耶穌又用比喻對他們說:
2መንግሥተ ሰማያት ለልጁ ሰርግ ያደረገ ንጉሥን ትመስላለች።
2“天國好像一個王,為兒子擺設婚筵。
3የታደሙትንም ወደ ሰርጉ ይጠሩ ዘንድ ባሮቹን ላከ ሊመጡም አልወደዱም።
3他派僕人去叫被邀請的人來參加婚筵。但他們不肯來。
4ደግሞ ሌሎችን ባሮች ልኮ። የታደሙትን። እነሆ፥ ድግሴን አዘጋጀሁ፥ ኮርማዎቼና የሰቡት ከብቶቼ ታርደዋል፥ ሁሉም ተዘጋጅቶአል፤ ወደ ሰርጉ ኑ በሉአቸው አለ።
4他再派另一些僕人去,說:‘你們告訴被邀請的人,我已經預備好了筵席,公牛和肥畜已經宰了,一切都預備妥當。來參加婚筵吧!’
5እነርሱ ግን ቸል ብለው አንዱ ወደ እርሻው፥ ሌላውም ወደ ንግዱ ሄደ፤
5但那些人卻不理會就走了;有的去耕田,有的去作買賣,
6የቀሩትም ባሮቹን ይዘው አንገላቱአቸው ገደሉአቸውም።
6其餘的抓住王的僕人,凌辱他們,並且把他們殺了。
7ንጉሡም ተቈጣ፥ ጭፍሮቹንም ልኮ እነዚያን ገዳዮች አጠፋ፤ ከተማቸውንም አቃጠለ።
7王就發怒,派兵消滅那些兇手,焚毀他們的城。
8በዚያን ጊዜ ባሮቹን። ሰርጉስ ተዘጋጅቶአል፥ ነገር ግን የታደሙት የማይገባቸው ሆኑ፤
8然後對僕人說:‘婚筵已經預備好了,只是被邀請的人不配。
9እንግዲህ ወደ መንገድ መተላለፊያ ሄዳችሁ ያገኛችሁትን ሁሉ ወደ ሰርጉ ጥሩ አለ።
9所以你們要到大路口,凡遇見的,都請來參加婚筵。’
10እነዚያም ባሮች ወደ መንገድ ወጥተው ያገኙትን ሁሉ ክፉዎችንም በጎዎችንም ሰበሰቡ፤ የሰርጉንም ቤት ተቀማጮች ሞሉት።
10“那些僕人就走到街上,把所有遇見的,不論好人壞人,都招聚了來,婚筵上就坐滿了人。
11ንጉሡም የተቀመጡትን ለማየት በገባ ጊዜ በዚያ የሰርግ ልብስ ያለበሰ አንድ ሰው አየና። ወዳጄ ሆይ፥
11王進來與赴筵的人見面,看見有一個人沒有穿著婚筵的禮服,
12የሰርግ ልብስ ሳትለብስ እንዴት ወደዚህ ገባህ? አለው እርሱም ዝም አለ።
12就對他說:‘朋友,你沒有婚筵的禮服,怎能進到這裡來呢?’他就無話可說。
13በዚያን ጊዜ ንጉሡ አገልጋዮቹን። እጁንና እግሩን አስራችሁ በውጭ ወዳለው ጨለማ አውጡት፤ በዚያ ልቅሶና ጥርስ ማፋጨት ይሆናል አለ።
13於是王對侍從說:‘把他的手和腳都綁起來,丟到外面的黑暗裡,在那裡必要哀哭切齒。’
14የተጠሩ ብዙዎች፥ የተመረጡ ግን ጥቂቶች ናቸውና።
14因為被召的人多,選上的人少。”
15ስለዚህ ፈሪሳውያን ሄዱና እንዴት አድርገው በነገር እንዲያጠምዱት ተማከሩ።
15以納稅的事問難耶穌(可12:13~17;路20:20~26)法利賽人就去商量,怎樣找耶穌的話柄來陷害他。
16ደቀ መዛሙርታቸውንም ከሄሮድስ ወገን ጋር ላኩበት፥ እነርሱም። መምህር ሆይ፥ እውነተኛ እንደ ሆንህ በእውነትም የእግዚአብሔርን መንገድ እንድታስተምር እናውቃለን፥ ለማንምም አታደላም፥ የሰውን ፊት አትመለከትምና፤
16他們派了自己的門徒和希律黨的人一同去問耶穌:“老師,我們知道你為人誠實,照著真理把 神的道教導人,不顧忌任何人,因為你不徇情面。
17እንግዲህ ምን ይመስልሃል? ንገረን ለቄሣር ግብር መስጠት ተፈቅዶአልን ወይስ አልተፈቀደም? አሉት።
17請把你的意見告訴我們,納稅給凱撒,可不可以呢?”
18ኢየሱስም ክፋታቸውን አውቆ። እናንተ ግብዞች፥ ስለ ምን ትፈትኑኛላችሁ?
18耶穌看出他們的惡意,就說:“虛偽的人,為甚麼試探我呢?
19የግብሩን ብር አሳዩኝ አለ። እነርሱም ዲናር አመጡለት።
19拿納稅的錢幣給我看看。”他們就拿了一個銀幣給他。
20እርሱም። ይህች መልክ ጽሕፈቲቱስ የማን ናት? አላቸው።
20耶穌問他們:“這是誰的像,誰的名號?”
21የቄሣር ነው አሉት። በዚያን ጊዜ። እንኪያስ የቄሣርን ለቄሣር የእግዚአብሔርንም ለእግዚአብሔር አስረክቡ አላቸው።
21他們回答:“凱撒的。”他就對他們說:“凱撒的應當歸給凱撒, 神的應當歸給 神。”
22ይህንም ሰምተው ተደነቁ፥ ትተውትም ሄዱ።
22他們聽了,十分驚奇,就離開他走了。
23በዚያን ቀን። ትንሣኤ ሙታን የለም የሚሉ ሰዱቃውያን ወደ እርሱ ቀረቡ፥
23人復活後不娶不嫁(可12:18~27;路20:27~40)撒都該人向來認為沒有復活的事。那一天,他們前來問耶穌:
24እንዲህም ብለው ጠየቁት። መምህር ሆይ፥ ሙሴ አንድ ሰው ልጅ ሳይወልድ ሲሞት ወንድሙ ሚስቱን አግብቶ ለወንድሙ ዘር ይተካ አለ።
24“老師,摩西說:‘如果一個人死了,沒有兒女,他的弟弟應該娶他的妻子,為哥哥立後。’
25ሰባት ወንድማማች በእኛ ዘንድ ነበሩ፤ ፊተኛውም ሚስት አግብቶ ሞተ፥ ዘርም ስለሌለው ሚስቱን ለወንድሙ ተወለት፤
25從前我們這裡有兄弟七人,頭一個結了婚,沒有孩子就死了,留下妻子給他的弟弟。
26እንዲሁ ደግሞ ሁለተኛው ሦስተኛውም፥ እስከ ሰባተኛው ድረስ።
26第二個、第三個直到第七個都是這樣。
27ከሁሉም በኋላ ሴቲቱ ሞተች።
27最後,那女人也死了。
28ሁሉ አግብተዋታልና በትንሣኤ ቀንስ፥ ከሰባቱ ለማናቸው ሚስት ትሆናለች?
28那麼,復活的時候,她是這七個人中哪一個的妻子呢?因為他們都娶過她。”
29ኢየሱስም መልሶ እንዲህ አላቸው። መጻሕፍትንና የእግዚአብሔርን ኃይል አታውቁምና ትስታላችሁ።
29耶穌回答他們:“你們錯了,因為你們不明白聖經,也不曉得 神的能力。
30በትንሣኤስ እንደ እግዚአብሔር መላእክት በሰማይ ይሆናሉ እንጂ አያገቡም አይጋቡምም።
30復活的時候,人們也不娶也不嫁,而是像天上的使者一樣。
31ስለ ትንሣኤ ሙታን ግን። እኔ የአብርሃም አምላክ፥ የይስሐቅም አምላክ የያዕቆብም አምላክ ነኝ የሚል ከእግዚአብሔር ዘንድ ወደ እናንተ የተባለውን አላነበባችሁምን? የሕያዋን አምላክ ነው እንጂ የሙታን አይደለም።
31關於死人復活的事, 神對你們講過:‘我是亞伯拉罕的 神,以撒的 神,雅各的 神’,你們沒有念過嗎? 神不是死人的 神,而是活人的 神。”
33ሕዝቡም ይህን ሰምተው በትምህርቱ ተገረሙ።
32
34ፈሪሳውያንም ሰዱቃውያንን ዝም እንዳሰኛቸው በሰሙ ጊዜ አብረው ተሰበሰቡ።
33群眾聽了他的教訓,就十分詫異。
35ከእነርሱም አንድ ሕግ አዋቂ ሊፈትነው።
34最重要的誡命(可12:28~31)法利賽人聽見耶穌使撒都該人無話可說,就聚集在一起。
36መምህር ሆይ፥ ከሕግ ማናቸይቱ ትእዛዝ ታላቅ ናት? ብሎ ጠየቀው።
35他們中間有一個律法家,試探耶穌說:
37ኢየሱስም እንዲህ አለው። ጌታ አምላክህን በፍጹም ልብህ በፍጹም ነፍስህም በፍጹም አሳብህም ውደድ።
36“老師,律法中哪一條誡命是最重要的呢?”
38ታላቂቱና ፊተኛይቱ ትእዛዝ ይህች ናት።
37他回答:“你要全心、全性、全意愛主你的 神。
39ሁለተኛይቱም ይህችን ትመስላለች፥ እርስዋም። ባልንጀራህን እንደ ነፍስህ ውደድ የምትለው ናት።
38這是最重要的第一條誡命。
40በእነዚህ በሁለቱ ትእዛዛት ሕጉም ሁሉ ነቢያትም ተሰቅለዋል።
39第二條也和它相似,就是要愛人如己。
41ፈሪሳውያንም ተሰብስበው ሳሉ፥ ኢየሱስ። ስለ ክርስቶስ ምን ይመስላችኋል? የማንስ ልጅ ነው? ብሎ ጠየቃቸው። የዳዊት ልጅ ነው አሉት።
40全部律法和先知書,都以這兩條誡命作為根據。”
43እርሱም። እንኪያስ ዳዊት። ጌታ ጌታዬን። ጠላቶችህን የእግርህ መረገጫ እስካደርግልህ ድረስ በቀኜ ተቀመጥ አለው ሲል እንዴት በመንፈስ ጌታ ብሎ ይጠራዋል?
41基督是大衛的子孫(可12:35~37;路20:41~44)法利賽人聚在一起的時候,耶穌問他們:
45ዳዊትስ ጌታ ብሎ ከጠራው፥ እንዴት ልጁ ይሆናል? አላቸው።
42“你們對基督的看法怎樣?他是誰的子孫呢?”他們回答:“大衛的子孫。”
46አንድም ቃል ስንኳ ይመልስለት ዘንድ የተቻለው የለም፥ ከዚያ ቀንም ጀምሮ ወደ ፊት ማንም ሊጠይቀው አልደፈረም።
43耶穌就說:“那麼大衛被聖靈感動,怎麼會稱他為主呢?他說:
44‘主對我的主說:你坐在我的右邊,等我把你的仇敵放在你的腳下。’
45“大衛既然稱他為主,他怎麼又是大衛的子孫呢?”
46沒有人能夠回答他。從那天起,也沒有人敢再問他。