Amharic: New Testament

聖經新譯本

Revelation

2

1በኤፌሶን ወዳለው ወደ ቤተ ክርስቲያን መልአክ እንዲህ ብለህ ጻፍ። በቀኝ እጁ ሰባቱን ከዋክብት የያዘው በሰባቱም የወርቅ መቅረዞች መካከል የሚሄደው እንዲህ ይላል።
1給以弗所教會的信“你要寫信給在以弗所教會的使者,說:‘那右手拿著七星,在七個金燈臺中間行走的,這樣說:
2ሥራህንና ድካምህን ትዕግሥትህንም አውቃለሁ፤ ክፉዎችንም ልትታገሥ እንዳትችል፥ እንዲሁም ሳይሆኑ። ሐዋርያት ነን የሚሉቱን መርምረህ ሐሰተኞች ሆነው እንዳገኘሃቸው አውቃለሁ፤
2我知道你的行為、你的勞苦、你的忍耐,也知道你不能容忍惡人。你也曾經試驗那些自稱是使徒,而其實不是使徒的人,看出他們是假的。
3ታግሠህማል፥ ስለ ስሜም ብለህ ጸንተህ አልደከምህም።
3你有忍耐,曾為我的名的緣故忍受一切,並不困倦。
4ዳሩ ግን የምነቅፍብህ ነገር አለኝ የቀደመውን ፍቅርህን ትተሃልና።
4然而有一件事我要責備你,就是你已經離棄了你起初的愛。
5እንግዲህ ከወዴት እንደ ወደቅህ አስብ ንስሐም ግባ የቀደመውንም ሥራህን አድርግ፤ አለዚያ እመጣብሃለሁ ንስሐም ባትገባ መቅረዝህን ከስፍራው እወስዳለሁ።
5所以,你應當回想你是從哪裡墜落的,並且要悔改,作起初所作的事。你若不悔改,我就要來到你那裡,把你的燈臺從原處移去。
6ነገር ግን ይህ አለህ፤ እኔ ደግሞ የምጠላውን የኒቆላውያንን ሥራ ጠልተሃልና።
6不過你有這一個優點,就是你恨惡尼哥拉黨的作為,那也是我所恨惡的。
7መንፈስ ለአብያተ ክርስቲያናት የሚለውን ጆሮ ያለው ይስማ። ድል ለነሣው በእግዚአብሔር ገነት ካለው ከሕይወት ዛፍ እንዲበላ እሰጠዋለሁ።
7聖靈向眾教會所說的話,有耳的就應當聽。得勝的,我必定把 神樂園裡生命樹的果子賜給他吃。’
8በሰምርኔስም ወዳለው ወደ ቤተ ክርስቲያን መልአክ እንዲህ ብለህ ጻፍ። ሞቶ የነበረው ሕያውም የሆነው ፊተኛውና መጨረሻው እንዲህ ይላል።
8給士每拿教會的信“你要寫信給在士每拿教會的使者,說:‘那首先的、末後的、曾經死去而又活過來的,這樣說:
9መከራህንና ድህነትህን አውቃለሁ፥ ነገር ግን ባለ ጠጋ ነህ፤ የሰይጣንም ማኅበር ናቸው እንጂ አይሁድ ሳይሆኑ። አይሁድ ነን የሚሉት የሚሳደቡትን ስድብ አውቃለሁ።
9我知道你的患難和貧窮,但你卻是富足的。我也知道那些自稱是猶太人所說毀謗的話,其實他們不是猶太人,而是撒但的黨徒。
10ልትቀበለው ያለህን መከራ አትፍራ። እነሆ፥ እንድትፈተኑ ዲያብሎስ ከእናንተ አንዳንዶቻችሁን በወኅኒ ሊያገባችሁ አለው፥ አሥር ቀንም መከራን ትቀበላላችሁ። እስከሞት ድረስ የታመንህ ሁን የሕይወትንም አክሊል እሰጥሃለሁ።
10你不要怕你將要受的苦。看哪!魔鬼將要把你們中間幾個人下在監裡,叫你們受試煉,你們要受患難十天。你要忠心至死,我就把那生命的冠冕賜給你。
11መንፈስ ለአብያተ ክርስቲያናት የሚለውን ጆሮ ያለው ይስማ። ድል የነሣው በሁለተኛው ሞት አይጐዳም።
11聖靈向眾教會所說的話,有耳的就應當聽。得勝的,決不會受第二次死的害。’
12በጴርጋሞንም ወዳለው ወደ ቤተ ክርስቲያን መልአክ እንዲህ ብለህ ጻፍ። በሁለት ወገን የተሳለ ስለታም ሰይፍ ያለው እንዲህ ይላል።
12給別迦摩教會的信“你要寫信給在別迦摩教會的使者,說:‘那有一把兩刃利劍的,這樣說:
13የሰይጣን ዙፋን ባለበት የምትኖርበትን አውቃለሁ፤ ስሜንም ትጠብቃለህ፥ ሰይጣንም በሚኖርበት፥ በእናንተ ዘንድ የተገደለው የታመነው ምስክሬ አንቲጳስ በነበረበት ዘመን እንኳ ሃይማኖቴን አልካድህም።
13我知道你居住的地方,就是撒但王座所在的地方。當我忠心的見證人安提帕在你們那裡,就是在撒但居住的地方被殺的那些日子,你還持守我的名,沒有否認對我的信仰。
14ዳሩ ግን ለጣዖት የታረደውን እንዲበሉና እንዲሴስኑ በእስራኤል ልጆች ፊት ማሰናከያን ሊያኖርባቸው ባላቅን ያስተማረ የበልዓምን ትምህርት የሚጠብቁ በዚያ ከአንተ ጋር ስላሉ፥ የምነቅፍብህ ጥቂት ነገር አለኝ።
14然而有幾件事我要責備你,因為在你那裡有些人持守巴蘭的教訓。這巴蘭曾經教導巴勒把絆腳石放在以色列人面前,叫他們吃祭過偶像的食物,並且行淫亂。
15እንዲሁ የኒቆላውያንን ትምህርት እንደ እነዚህ የሚጠብቁ ሰዎች ከአንተ ጋር ደግሞ አሉ።
15同樣,你也有些人持守尼哥拉黨的教訓。
16እንግዲህ ንስሐ ግባ፤ አለዚያ ፈጥኜ እመጣብሃለሁ፥ በአፌም ሰይፍ እዋጋቸዋለሁ።
16所以,你應當悔改;如果不悔改,我就很快地來到你們那裡,用我口中的劍跟他們作戰。
17መንፈስ ለአብያተ ክርስቲያናት የሚለውን ጆሮ ያለው ይስማ። ድል ለነሣው ከተሰወረ መና እሰጠዋለሁ፥ ነጭ ድንጋይንም እሰጠዋለሁ፥ በድንጋዩም ላይ ከተቀበለው በቀር አንድ ስንኳ የሚያውቀው የሌለ አዲስ ስም ተጽፎአል።
17聖靈向眾教會所說的話,有耳的就應當聽。得勝的,我必定把那隱藏的嗎哪賜給他,並且賜他一塊白石,石上寫著新的名字,這名字除了那領受的人以外,是沒有人能知道的。’
18በትያጥሮንም ወዳለው ወደ ቤተ ክርስቲያን መልአክ እንዲህ ብለህ ጻፍ። እንደ እሳት ነበልባል የሆኑ ዓይኖች ያሉት በእቶንም የነጠረ የጋለ ናስ የሚመስሉ እግሮች ያሉት የእግዚአብሔር ልጅ እንዲህ ይላል።
18給推雅推拉教會的信“你要寫信給在推雅推拉教會的使者,說:‘ 神的兒子,那眼睛像火燄、兩腳像光銅的,這樣說:
19ሥራህንና ፍቅርህን እምነትህንም አገልግሎትህንም ትዕግሥትህንም ከፊተኛውም ሥራህ ይልቅ የኋለኛው እንዲበዛ አውቃለሁ።
19我知道你的行為,你的愛心、信心、服侍和忍耐,也知道你後來所作的比先前的還要多。
20ዳሩ ግን። ነቢይ ነኝ የምትለውን ባሪያዎቼንም እንዲሴስኑና ለጣዖት የታረደውን እንዲበሉ የምታስተምረውንና የምታስተውን ያችን ሴት ኤልዛቤልን ስለምትተዋት የምነቅፍብህ ነገር አለኝ፤
20然而有一件事我要責備你,就是你容讓那自稱是先知的婦人耶洗別,教導和引誘我的眾僕人行淫亂,吃祭過偶像的食物。
21ንስሐም እንድትገባ ጊዜ ሰጠኋት ከዝሙትዋም ንስሐ እንድትገባ አልወደደችም።
21我曾給她時間,讓她悔改,她卻不肯為她的淫行悔改。
22እነሆ፥ በአልጋ ላይ እጥላታለሁ፥ ከእርስዋም ጋር የሚያመነዝሩትን ከሥራዋ ንስሐ ባይገቡ በታላቅ መከራ እጥላቸዋለሁ፤
22看哪,我要把她拋在大患難的床上;那些跟她行淫亂的人,如果不為她的行為悔改,我也要把他們拋在大患難中。
23ልጆችዋንም በሞት እገድላቸዋለሁ፤ አብያተ ክርስቲያናትም ሁሉ ኵላሊትንና ልብን የምመረምር እኔ እንደ ሆንሁ ያውቃሉ፥ ለእያንዳንዳችሁም እንደ ሥራችሁ እሰጣችኋለሁ።
23我必以死亡擊殺她的兒女;眾教會就都知道我是察驗人肺腑心腸的,我要照著你們的行為報應你們各人。
24ዳሩ ግን ይህን ትምህርት ለማትይዙ ሁሉ የሰይጣንንም ጥልቅ ነገር እነርሱ እንደሚሉት ለማታውቁ ለእናንተ በትያጥሮን ለቀራችሁት እላለሁ፤ ሌላ ሸክም አልጭንባችሁም፥
24至於你們其餘在推雅推拉的人,就是不跟從那教訓,不認識所謂撒但深奧的事的人,我告訴你們,我不會把別的重擔放在你們身上。
25ነገር ግን እስክመጣ ድረስ ያላችሁን ጠብቁ።
25不過,你們要持守已經得著的,直到我來。
26ድል ለነሣውና እስከ መጨረሻም ሥራዬን ለጠበቀው እኔ ደግሞ ከአባቴ እንደ ተቀበልሁ በአሕዛብ ላይ ሥልጣንን እሰጠዋለሁ፥ በብረትም በትር ይገዛቸዋል፥ እንደ ሸክላ ዕቃም ይቀጠቀጣሉ፤
26得勝的,又遵守我的旨意到底的,我必把統治列國的權柄賜給他,
28የንጋትንም ኮከብ እሰጠዋለሁ።
27他必用鐵杖治理他們,好像打碎陶器一樣粉碎他們,(“我必把……粉碎他們”引自詩2:8~9)
29መንፈስ ለአብያተ ክርስቲያናት የሚለውን ጆሮ ያለው ይስማ።
28好像我從父領受了權柄一樣;我還要把晨星賜給他。
29聖靈向眾教會所說的話,有耳的就應當聽。’”