Amharic: New Testament

聖經新譯本

Revelation

22

1በአደባባይዋም መካከል ከእግዚአብሔርና ከበጉ ዙፋን የሚወጣውን እንደ ብርሌ የሚያንጸባርቀውን የሕይወትን ውኃ ወንዝ አሳየኝ።
1天使又指示我一道明亮如水晶的生命水的河流,從 神和羊羔的寶座那裡流出來,
2በወንዙም ወዲያና ወዲህ በየወሩ እያፈራ አሥራ ሁለት ፍሬ የሚሰጥ የሕይወት ዛፍ ነበረ፥ የዛፉም ቅጠሎች ለሕዝብ መፈወሻ ነበሩ።
2經過城裡的街道。河的兩邊有生命樹,結十二次果子,每月都結果子;樹葉可以醫治列國。
3ከእንግዲህም ወዲህ መርገም ከቶ አይሆንም። የእግዚአብሔርና የበጉም ዙፋን በእርስዋ ውስጥ ይሆናል፥ ባሪያዎቹም ያመልኩታል፥ ፊቱንም ያያሉ፥
3所有咒詛都不再有了。城裡有 神和羊羔的寶座,他的僕人都要事奉他,
4ስሙም በግምባሮቻቸው ይሆናል።
4也要見他的面。他的名字必寫在他們的額上。
5ከእንግዲህም ወዲህ ሌሊት አይሆንም፥ ጌታ አምላክም በእነርሱ ላይ ያበራላቸዋልና የመብራት ብርሃንና የፀሐይ ብርሃን አያስፈልጋቸውም፤ ለዘላለምም እስከ ዘላለም ይነግሣሉ።
5不再有黑夜了,他們也不需要燈光或日光了,因為主 神要光照他們。他們要作王,直到永永遠遠。
6እርሱም። እነዚህ ቃሎች የታመኑና እውነተኛዎች ናቸው፥ የነቢያትም መናፍስት ጌታ አምላክ በቶሎ ሊሆን የሚገባውን ነገር ለባሪያዎቹ እንዲያሳይ መልአኩን ሰደደ።
6耶穌再來天使對我說:“這些話是可信的、真實的!主,就是眾先知之靈的 神,差遣了他的天使,把那快要發生的事,指示他的僕人。”
7እነሆም፥ በቶሎ እመጣለሁ። የዚህን መጽሐፍ ትንቢት ቃል የሚጠብቅ ብፁዕ ነው አለኝ።
7“看哪!我必快來!那遵守這書上預言的人是有福的!”
8ይህንም ያየሁትና የሰማሁት እኔ ዮሐንስ ነኝ። በሰማሁትና ባየሁትም ጊዜ ይህን ባሳየኝ በመልአኩ እግር ፊት እሰግድ ዘንድ ተደፋሁ።
8聽見又看見了這些事的,就是我約翰。我聽見又看見了之後,就俯伏在指示我這些事的天使腳前要拜他。
9እርሱም። እንዳታደርገው ተጠንቀቅ፤ ከአንተ ጋር ከወንድሞችህም ከነቢያት ጋር የዚህንም መጽሐፍ ቃል ከሚጠብቁ ጋር አብሬ ባሪያ ነኝ፤ ለእግዚአብሔር ስገድ አለኝ።
9他對我說:“千萬不可以這樣!我和你,以及你的弟兄眾先知,還有那些遵守這書上的話的人,都是同作僕人的。你應當敬拜 神。”
10ለእኔም። ዘመኑ ቀርቦአልና የዚህን መጽሐፍ ትንቢት ቃል በማኅተም አትዝጋው።
10他又對我說:“不要封住這書上的預言,因為時候近了。
11ዓመፀኛው ወደ ፊት ያምፅ፥ ርኵሱም ወደ ፊት ይርከስ፥ ጻድቁም ወደ ፊት ጽድቅ ያድርግ፥ ቅዱሱም ወደፊት ይቀደስ አለ።
11不義的,要他仍舊不義;污穢的,要他仍舊污穢;行義的,要他仍舊行義;聖潔的,要他仍舊聖潔。”
12እነሆ፥ በቶሎ እመጣለሁ፥ ለእያንዳንዱም እንደ ሥራው መጠን እከፍል ዘንድ ዋጋዬ ከእኔ ጋር አለ።
12“看哪,我必快來!賞賜在我,我要照著各人所行的報應他。
13አልፋና ዖሜጋ፥ ፊተኛውና ኋለኛው፥ መጀመሪያውና መጨረሻው እኔ ነኝ።
13我是阿拉法,是俄梅格;我是首先的,也是末後的;我是創始的,也是成終的。”
14ወደ ሕይወት ዛፍ ለመድረስ ሥልጣን እንዲኖራቸው በደጆችዋም ወደ ከተማይቱም እንዲገቡ ልብሳቸውን የሚያጥቡ ብፁዓን ናቸው።
14那些洗淨自己袍子的人是有福的!他們可以有權到生命樹那裡,也可以從門進到城裡。
15ውሻዎችና አስማተኞች ሴሰኛዎችም ነፍሰ ገዳዮችም ጣዖትንም የሚያመልኩት ውሸትንም የሚወዱና የሚያደርጉ ሁሉ በውጭ አሉ።
15在城外,有那些狗,那些行邪術的、淫亂的、殺人的、拜偶像的,以及所有喜愛說謊的和實行說謊的人。
16እኔ ኢየሱስ በአብያተ ክርስቲያናት ዘንድ ይህን እንዲመሰክርላችሁ መልአኬን ላክሁ። እኔ የዳዊት ሥርና ዘር ነኝ፥ የሚያበራም የንጋት ኮከብ ነኝ።
16“差遣了我的使者、為眾教會向你們證明這些事的,就是我耶穌。我是大衛的根,又是他的後裔,我是明亮的晨星。”
17መንፈሱና ሙሽራይቱም። ና ይላሉ። የሚሰማም። ና ይበል። የተጠማም ይምጣ፥ የወደደም የሕይወትን ውኃ እንዲያው ይውሰድ።
17聖靈和新娘都說:“來!”聽見的人也要說:“來!”口渴的人也要來!願意的人都要白白接受生命的水!
18በዚህ መጽሐፍ የተጻፈውን የትንቢት ቃል ለሚሰማ ሁሉ እኔ እመሰክራለሁ፤ ማንም በዚህ ላይ አንዳች ቢጨምር እግዚአብሔር በዚህ መጽሐፍ የተጻፉትን መቅሠፍቶች ይጨምርበታል፤
18我警告所有聽見這書上預言的人:如果有人在這些預言上加添甚麼, 神必把寫在這書上的災難加在他身上。
19ማንምም በዚህ በትንቢት መጽሐፍ ከተጻፉት ቃሎች አንዳች ቢያጎድል፥ በዚህ መጽሐፍ ከተጻፉት ከሕይወት ዛፍና ከቅድስቲቱ ከተማ እግዚአብሔር ዕድሉን ያጎድልበታል።
19如果有人從這書上的預言刪減甚麼, 神必從這書上所記的生命樹和聖城刪去他的分。
20ይህን የሚመሰክር። አዎን፥ በቶሎ እመጣለሁ ይላል። አሜን፥ ጌታ ኢየሱስ ሆይ፥ ና።
20證明這些事的那一位說:“是的,我必快來!”阿們!主耶穌啊,請你來吧!
21የጌታችን የኢየሱስ ክርስቶስ ጸጋ ከሁላችን ጋር ይሁን፤ አሜን።
21願主耶穌的恩惠與所有的聖徒同在!阿們!