1ወንድሞች ሆይ፥ የልቤ በጎ ፈቃድና ስለ እስራኤል ወደ እግዚአብሔር ልመናዬ እንዲድኑ ነው።
1弟兄們,我心裡切切盼望的,並且為以色列人向 神祈求的,是要他們得救。
2በእውቀት አይቅኑ እንጂ ለእግዚአብሔር እንዲቀኑ እመሰክርላቸዋለሁና።
2我可以為他們作證,他們對 神有熱心,但不是按著真見識;
3የእግዚአብሔርን ጽድቅ ሳያውቁ የራሳቸውንም ጽድቅ ሊያቆሙ ሲፈልጉ፥ ለእግዚአብሔር ጽድቅ አልተገዙም።
3他們既然不明白 神的義,而又企圖建立自己的義,就不服 神的義了。
4የሚያምኑ ሁሉ ይጸድቁ ዘንድ ክርስቶስ የሕግ ፍጻሜ ነውና።
4因為律法的終極就是基督,使所有信的人都得著義。
5ሙሴ ከሕግ የሆነውን ጽድቅ የሚያደርገው ሰው በእርሱ በሕይወት እንዲኖር ጽፎአልና።
5求告主名的都必得救論到出於律法的義,摩西寫著說:“遵行這些事的人就必因這些事而活。”
6ከእምነት የሆነ ጽድቅ ግን እንዲህ ይላል። በልብህ። ማን ወደ ሰማይ ይወጣል? አትበል፤ ይህ ክርስቶስን ለማውረድ ነው፤
6但那出於信心的義卻這樣說:“你心裡不要說:‘誰要升到天上去呢?’(就是要把基督領下來,)
7ወይም። በልብህ። ወደ ጥልቁ ማን ይወርዳል? አትበል፤ ይህ ክርስቶስን ከሙታን ለማውጣት ነው።
7或是說:‘誰要下到深淵去呢?’(就是要把基督從死人中領上來。)”
8ነገር ግን ምን ይላል? በአፍህ በልብህም ሆኖ ቃሉ ቀርቦልሃል፤ ይህም የምንሰብከው የእምነት ቃል ነው።
8然而那出於信心的義還說甚麼呢?“這話與你相近,在你口裡,也在你心裡。”這話就是我們所傳信心的信息。
9ኢየሱስ ጌታ እንደ ሆነ በአፍህ ብትመሰክር እግዚአብሔርም ከሙታን እንዳስነሣው በልብህ ብታምን ትድናለህና፤
9你若口裡認耶穌為主,心裡信 神使他從死人中復活,就必得救;
10ሰው በልቡ አምኖ ይጸድቃልና በአፉም መስክሮ ይድናልና።
10因為心裡相信就必稱義,用口承認就必得救。
11መጽሐፍ። በእርሱ የሚያምን ሁሉ አያፍርም ይላልና።
11經上說:“所有信靠他的人,必不致失望。”
12በአይሁዳዊና በግሪክ ሰው መካከል ልዩነት የለምና፤ አንዱ ጌታ የሁሉ ጌታ ነውና፥ ለሚጠሩትም ሁሉ ባለ ጠጋ ነው፤
12其實並不分猶太人和希臘人,因為大家同有一位主;他厚待所有求告他的人,
13የጌታን ስም የሚጠራ ሁሉ ይድናልና።
13因為“凡求告主名的,都必得救。”
14እንግዲህ ያላመኑበትን እንዴት አድርገው ይጠሩታል? ባልሰሙትስ እንዴት ያምናሉ? ያለ ሰባኪስ እንዴት ይሰማሉ?
14然而,人還沒有信他,怎能求告他呢?沒有聽見他,怎能信他呢?沒有人傳揚,怎能聽見呢?
15መልካሙን የምሥራች የሚያወሩ እግሮቻቸው እንዴት ያማሩ ናቸው ተብሎ እንደ ተጻፈ ካልተላኩ እንዴት ይሰብካሉ?
15如果沒有蒙差遣,怎能傳揚呢?如經上所記:“那些傳美事報喜訊的人,他們的腳蹤多麼美!”
16ነገር ግን ሁሉ ለምሥራቹ ቃል አልታዘዙም። ኢሳይያስ። ጌታ ሆይ፥ ምስክርነታችንን ማን አመነ? ብሎአልና።
16但並不是所有的人都順從福音,因為以賽亞說:“主啊,我們所傳的,有誰信呢?”
17እንግዲያስ እምነት ከመስማት ነው መስማትም በእግዚአብሔር ቃል ነው።
17可見信心是從所聽的道來的,所聽的道是藉著基督的話來的。
18ዳሩ ግን። ባይሰሙ ነው ወይ? እላለሁ። በእውነት። ድምፃቸው በምድር ሁሉ ላይ ቃላቸውም እስከ ዓለም ዳርቻ ወጣ።
18但是我要說,他們沒有聽見嗎?他們的確聽見了,如經上所記:“他們的聲音傳遍全地,他們的言語傳到地極。”
19ነገር ግን። እስራኤል ባያውቁ ነው ወይ? እላለሁ። ሙሴ አስቀድሞ። እኔ ሕዝብ በማይሆነው አስቀናችኋለሁ በማያስተውልም ሕዝብ አስቆጣችኋለሁ
19我再說:以色列人真的不明白嗎?首先,摩西說:“我要使你們對那不是子民的生嫉妒,對那無知的民族起忿怒。”
20ብሎአል። ኢሳይያስም ደፍሮ። ላልፈለጉኝ ተገኘሁ፥ ላልጠየቁኝም ተገለጥሁ አለ።
20後來,以賽亞也放膽地說:“沒有尋找我的,我讓他們找到;沒有求問我的,我向他們顯現。”
21ስለ እስራኤል ግን። ቀኑን ሁሉ ወደማይታዘዝና ወደሚቃወም ሕዝብ እጆቼን ዘረጋሁ ይላል።
21論到以色列人,他卻說:“我整天向那悖逆頂嘴的子民伸開雙手。”