Amharic: New Testament

American Standard Version

John

7

1ከዚህም በኋላ ኢየሱስ አይሁድ ሊገድሉት ይፈልጉ ስለ ነበር በይሁዳ ሊመላለስ አይወድም ነበርና በገሊላ ይመላለስ ነበር።
1And after these things Jesus walked in Galilee: for he would not walk in Judaea, because the Jews sought to kill him.
2የአይሁድም የዳስ በዓል ቀርቦ ነበር።
2Now the feast of the Jews, the feast of tabernacles, was at hand.
3እንግዲህ ወንድሞቹ። ደቀ መዛሙርትህ ደግሞ የምታደርገውን ሥራ እንዲያዩ ከዚህ ተነሣና ወደ ይሁዳ ሂድ፤
3His brethren therefore said unto him, Depart hence, and go into Judaea, that thy disciples also may behold thy works which thou doest.
4ራሱ ሊገለጥ እየፈለገ በስውር የሚሠራ የለምና። እነዚህን ብታደርግ ራስህን ለዓለም ግለጥ አሉት።
4For no man doeth anything in secret, and himself seeketh to be known openly. If thou doest these things, manifest thyself to the world.
5ወንድሞቹ ስንኳ አላመኑበትም ነበርና።
5For even his brethren did not believe on him.
6ኢየሱስም እንዲህ አላቸው። ጊዜዬ ገና አልደረሰም፥ ጊዜያችሁ ግን ዘወትር የተመቸ ነው።
6Jesus therefore saith unto them, My time is not yet come; but your time is always ready.
7ዓለም እናንተን ሊጠላ አይቻለውም፤ እኔ ግን ሥራው ክፉ መሆኑን እመሰክርበታለሁና እኔን ይጠላኛል።
7The world cannot hate you; but me it hateth, because I testify of it, that its works are evil.
8እናንተ ወደዚህ በዓል ውጡ፤ እኔስ ጊዜዬ ገና ስላልተፈጸመ ወደዚህ በዓል ገና አልወጣም።
8Go ye up unto the feast: I go not up unto this feast; because my time is not yet fulfilled.
9ይህንም አላቸውና በገሊላ ቀረ።
9And having said these things unto them, he abode [still] in Galilee.
10ወንድሞቹ ግን ወደ በዓሉ ከወጡ በኋላ በዚያን ጊዜ እርሱ ደግሞ በግልጥ ሳይሆን ተሰውሮ ወጣ።
10But when his brethren were gone up unto the feast, then went he also up, not publicly, but as it were in secret.
11አይሁድም። እርሱ ወዴት ነው? እያሉ በበዓሉ ይፈልጉት ነበር።
11The Jews therefore sought him at the feast, and said, Where is he?
12በሕዝብም መካከል ስለ እርሱ ብዙ ማንጐራጐር ነበረ፤ አንዳንዱም። ደግ ሰው ነው፤ ሌሎች ግን። አይደለም፥ ሕዝቡን ግን ያስታል ይሉ ነበር።
12And there was much murmuring among the multitudes concerning him: some said, He is a good man; others said, Not so, but he leadeth the multitude astray.
13ዳሩ ግን አይሁድን ስለ ፈሩ ማንም ስለ እርሱ በግልጥ አይናገርም ነበር።
13Yet no man spake openly of him for fear of the Jews.
14አሁንም በበዓሉ እኩሌታ ኢየሱስ ወደ መቅደስ ወጥቶ ያስተምር ነበር።
14But when it was now the midst of the feast Jesus went up into the temple, and taught.
15አይሁድም። ይህ ሰው ሳይማር መጻሕፍትን እንዴት ያውቃል? ብለው ይደነቁ ነበር።
15The Jews therefore marvelled, saying, How knoweth this man letters, having never learned?
16ስለዚህ ኢየሱስ መለሰ እንዲህም አላቸው። ትምህርቴስ ከላከኝ ነው እንጂ ከእኔ አይደለም፤
16Jesus therefore answered them and said, My teaching is not mine, but his that sent me.
17ፈቃዱን ሊያደርግ የሚወድ ቢኖር፥ እርሱ ይህ ትምህርት ከእግዚአብሔር ቢሆን ወይም እኔ ከራሴ የምናገር ብሆን ያውቃል።
17If any man willeth to do his will, he shall know of the teaching, whether it is of God, or [whether] I speak from myself.
18ከራሱ የሚናገር የራሱን ክብር ይፈልጋል፤ የላከውን ክብር የሚፈልግ ግን እርሱ እውነተኛ ነው በእርሱም ዓመፃ የለበትም።
18He that speaketh from himself seeketh his own glory: but he that seeketh the glory of him that sent him, the same is true, and no unrighteousness is in him.
19ሙሴ ሕግን አልሰጣችሁምን? ከእናንተ ግን ሕግን የሚያደርግ አንድ ስንኳ የለም። ልትገድሉኝ ስለ ምን ትፈልጋላችሁ?
19Did not Moses give you the law, and [yet] none of you doeth the law? Why seek ye to kill me?
20ሕዝቡ መለሱና። ጋኔን አለብህ፤ ማን ሊገድልህ ይፈልጋል? አሉት።
20The multitude answered, Thou hast a demon: who seeketh to kill thee?
21ኢየሱስ መለሰ አላቸውም። አንድ ሥራ አደረግሁ ሁላችሁም ታደንቃላችሁ።
21Jesus answered and said unto them, I did one work, and ye all marvel because thereof.
22ስለዚህ ሙሴ መገረዝን ሰጣችሁ፤ ከአባቶችም ነው እንጂ ከሙሴ አይደለም፤ በሰንበትም ሰውን ትገርዛላችሁ።
22Moses hath given you circumcision (not that it is of Moses, but of the fathers); and on the sabbath ye circumcise a man.
23የሙሴ ሕግ እንዳይሻር ሰው በሰንበት መገረዝን የሚቀበል ከሆነስ ሰውን ሁለንተናውን በሰንበት ጤናማ ስላደረግሁ ትቈጡኛላችሁን?
23If a man receiveth circumcision on the sabbath, that the law of Moses may not be broken; are ye wroth with me, because I made a man every whit whole on the sabbath?
24ቅን ፍርድ ፍረዱ እንጂ በመልክ አትፍረዱ።
24Judge not according to appearance, but judge righteous judgment.
25እንግዲህ ከኢየሩሳሌም ሰዎች አንዳንዶቹ እንዲህ አሉ። ሊገድሉት የሚፈልጉት ይህ አይደለምን?
25Some therefore of them of Jerusalem said, Is not this he whom they seek to kill?
26እነሆም፥ በግልጥ ይናገራል አንዳችም አይሉትም። አለቆቹ ይህ ሰው በእውነት ክርስቶስ እንደ ሆነ በእውነት አወቁን?
26And lo, he speaketh openly, and they say nothing unto him. Can it be that the rulers indeed know that this is the Christ?
27ነገር ግን ይህን ከወዴት እንደ ሆነ አውቀናል፤ ክርስቶስ ሲመጣ ግን ከወዴት እንደ ሆነ ማንም አያውቅም።
27Howbeit we know this man whence he is: but when the Christ cometh, no one knoweth whence he is.
28እንግዲህ ኢየሱስ በመቅደስ ሲያስተምር። እኔንም ታውቁኛላችሁ ከወዴትም እንደ ሆንሁ ታውቃላችሁ፤ እኔም በራሴ አልመጣሁም ነገር ግን እናንተ የማታውቁት የላከኝ እውነተኛ ነው፤
28Jesus therefore cried in the temple, teaching and saying, Ye both know me, and know whence I am; and I am not come of myself, but he that sent me is true, whom ye know not.
29እኔ ግን ከእርሱ ዘንድ ነኝ እርሱም ልኮኛልና አውቀዋለሁ ብሎ ጮኸ።
29I know him; because I am from him, and he sent me.
30ስለዚህ ሊይዙት ይፈልጉ ነበር፤ ነገር ግን ጊዜው ገና ስላልደረሰ ማንም እጁን አልጫነበትም።
30They sought therefore to take him: and no man laid his hand on him, because his hour was not yet come.
31ከሕዝቡ ግን ብዙዎች አመኑበትና። ክርስቶስ በመጣ ጊዜ ይህ ካደረጋቸው ምልክቶች ይልቅ ያደርጋልን? አሉ።
31But of the multitude many believed on him; and they said, When the Christ shall come, will he do more signs than those which this man hath done?
32ፈሪሳውያንም ሕዝቡ ሰለ እርሱ እንደዚህ ሲያንጐራጕሩ ሰሙ፤ የካህናት አለቆችም ፈሪሳውያም ሊይዙት ሎሌዎችን ላኩ።
32The Pharisees heard the multitude murmuring these things concerning him; and the chief priests and the Pharisees sent officers to take him.
33ኢየሱስም። ገና ጥቂት ጊዜ ከእናንተ ጋር እቆያለሁ ወደ ላከኝም እሄዳለሁ።
33Jesus therefore said, Yet a little while am I with you, and I go unto him that sent me.
34ትፈልጉኛላችሁ አታገኙኝምም፤ እኔም ወዳለሁበት እናንተ ልትመጡ አትችሉም አለ።
34Ye shall seek me, and shall not find me: and where I am, ye cannot come.
35እንግዲህ አይሁድ። እኛ እንዳናገኘው ይህ ወዴት ይሄድ ዘንድ አለው? በግሪክ ሰዎች መካከል ተበትነው ወደሚኖሩት ሊሄድና የግሪክን ሰዎች ሊያስተምር አለውን?
35The Jews therefore said among themselves, Whither will this man go that we shall not find him? will he go unto the Dispersion among the Greeks, and teach the Greeks?
36እርሱ። ትፈልጉኛላችሁ አታገኙኝምም እኔም ወዳለሁበት እናንተ ልትመጡ አትችሉም የሚለው ይህ ቃል ምንድር ነው? ብለው እርስ በርሳቸው ተነጋገሩ።
36What is this word that he said, Ye shall seek me, and shall not find me; and where I am, ye cannot come?
37ከበዓሉም በታላቁ በኋለኛው ቀን ኢየሱስ ቆሞ። ማንም የተጠማ ቢኖር ወደ እኔ ይምጣና ይጠጣ።
37Now on the last day, the great [day] of the feast, Jesus stood and cried, saying, If any man thirst, let him come unto me and drink.
38በእኔ የሚያምን መጽሐፍ እንዳለ፥ የሕይወት ውኃ ወንዝ ከሆዱ ይፈልቃል ብሎ ጮኸ።
38He that believeth on me, as the scripture hath said, from within him shall flow rivers of living water.
39ይህን ግን በእርሱ የሚያምኑ ሊቀበሉት ስላላቸው ስለ መንፈስ ተናገረ፤ ኢየሱስ ገና ስላልከበረ መንፈስ ገና አልወረደም ነበርና።
39But this spake he of the Spirit, which they that believed on him were to receive: for the Spirit was not yet [given]; because Jesus was not yet glorified.
40ስለዚህ ከሕዝቡ አያሌ ሰዎች ይህን ቃል ሲሰሙ። ይህ በእውነት ነቢዩ ነው አሉ፤
40[Some] of the multitude therefore, when they heard these words, said, This is of a truth the prophet.
41ሌሎች። ይህ ክርስቶስ ነው አሉ፤ ሌሎች ግን። ክርስቶስ በእውኑ ከገሊላ ይመጣልን?
41Others said, This is the Christ. But some said, What, doth the Christ come out of Galilee?
42ክርስቶስ ከዳዊት ዘር ዳዊትም ከነበረባት መንደር ከቤተ ልሔም እንዲመጣ መጽሐፍ አላለምን? አሉ።
42Hath not the scripture said that the Christ cometh of the seed of David, and from Bethlehem, the village where David was?
43እንግዲህ ከእርሱ የተነሣ በሕዝቡ መካከል መለያየት ሆነ፤
43So there arose a division in the multitude because of him.
44ከእነርሱም አንዳንዶቹ ሊይዙት ወደዱ ነገር ግን እጁን ማንም አልጫነበትም።
44And some of them would have taken him; but no man laid hands on him.
45ሎሌዎቹም ወደ ካህናት አለቆችና ወደ ፈሪሳውያን መጡ፤ እነዚያም። ያላመጣችሁት ስለ ምን ነው? አሉአቸው።
45The officers therefore came to the chief priests and Pharisees; and they said unto them, Why did ye not bring him?
46ሎሌዎቹ። እንደዚህ ሰው ማንም እንዲሁ ከቶ አልተናገረም ብለው መለሱ።
46The officers answered, Never man so spake.
47እንግዲህ ፈሪሳውያን። እናንተ ደግሞ ሳታችሁን?
47The Pharisees therefore answered them, Are ye also led astray?
48ከአለቆች ወይስ ከፈሪሳውያን በእርሱ ያመነ አለን?
48Hath any of the rulers believed on him, or of the Pharisees?
49ነገር ግን ሕግን የማያውቀው ይህ ሕዝብ ርጉም ነው ብለው መለሱላቸው።
49But this multitude that knoweth not the law are accursed.
50ከእነርሱ አንዱ በሌሊት ቀድሞ ወደ እርሱ መጥቶ የነበረ ኒቆዲሞስ።
50Nicodemus saith unto them (he that came to him before, being one of them),
51ሕጋችን አስቀድሞ ከእርሱ ሳይሰማ ምንስ እንዳደረገ ሳያውቅ በሰው ይፈርዳልን? አላቸው።
51Doth our law judge a man, except it first hear from himself and know what he doeth?
52እነርሱም መለሱና። አንተም ደግሞ ከገሊላ ነህን? ነቢይ ከገሊላ እንዳይነሣ መርምርና እይ አሉት።
52They answered and said unto him, Art thou also of Galilee? Search, and see that out of Galilee ariseth no prophet.
53እያንዳንዱም ወደ ቤቱ ሄደ።
53And they went every man unto his own house: