Amharic: New Testament

American Standard Version

Luke

1

1የከበርህ ቴዎፍሎስ ሆይ፥ ከመጀመሪያው በዓይን ያዩትና የቃሉ አገልጋዮች የሆኑት እንዳስተላለፉልን፥ በኛ ዘንድ ስለ ተፈጸመው ነገር ብዙዎች ታሪክን በየተራው ለማዘጋጀት ስለ ሞከሩ፥ እኔ ደግሞ ስለ ተማርኸው ቃል እርግጡን እንድታውቅ በጥንቃቄ ሁሉን ከመጀመሪያው ተከትዬ በየተራው ልጽፍልህ መልካም ሆኖ ታየኝ።
1Forasmuch as many have taken in hand to draw up a narrative concerning those matters which have been fulfilled among us,
5በይሁዳ ንጉሥ በሄሮድስ ዘመን ከአብያ ክፍል የሆነ ዘካርያስ የሚባል አንድ ካህን ነበረ፤ ሚስቱም ከአሮን ልጆች ነበረች፥ ስምዋም ኤልሳቤጥ ነበረ።
2even as they delivered them unto us, who from the beginning were eyewitnesses and ministers of the word,
6ሁለቱም በጌታ ትእዛዝና ሕግጋት ሁሉ ያለ ነቀፋ እየሄዱ በእግዚአብሔር ፊት ጻድቃን ነበሩ።
3it seemed good to me also, having traced the course of all things accurately from the first, to write unto thee in order, most excellent Theophilus;
7ኤልሳቤጥም መካን ነበረችና ልጅ አልነበራቸውም፤ ሁለቱም በዕድሜያቸው አርጅተው ነበር።
4that thou mightest know the certainty concerning the things wherein thou wast instructed.
8እርሱም በክፍሉ ተራ በእግዚአብሔር ፊት ሲያገለግል፥
5There was in the days of Herod, king of Judaea, a certain priest named Zacharias, of the course of Abijah: and he had a wife of the daughters of Aaron, and her name was Elisabeth.
9እንደ ካህናት ሥርዓት ወደ ጌታ ቤተ መቅደስ ገብቶ ለማጠን ዕጣ ደረሰበት።
6And they were both righteous before God, walking in all the commandments and ordinances of the Lord blameless.
10በዕጣንም ጊዜ ሕዝቡ ሁሉ በውጭ ቆመው ይጸልዩ ነበር።
7And they had no child, because that Elisabeth was barren, and they both were [now] well stricken in years.
11የጌታም መልአክ በዕጣኑ መሠዊያ ቀኝ ቆሞ ታየው።
8Now it came to pass, while he executed the priest's office before God in the order of his course,
12ዘካርያስም ባየው ጊዜ ደነገጠ፥ ፍርሃትም ወደቀበት።
9according to the custom of the priest's office, his lot was to enter into the temple of the Lord and burn incense.
13መልአኩም እንዲህ አለው። ዘካርያስ ሆይ፥ ጸሎትህ ተሰምቶልሃልና አትፍራ ሚስትህ ኤልሳቤጥም ወንድ ልጅ ትወልድልሃለች፥ ስሙንም ዮሐንስ ትለዋለህ።
10And the whole multitude of the people were praying without at the hour of incense.
14ደስታና ተድላም ይሆንልሃል፥ በመወለዱም ብዙዎች ደስ ይላቸዋል።
11And there appeared unto him an angel of the Lord standing on the right side of altar of incense.
15በጌታ ፊት ታላቅ ይሆናልና፥ የወይን ጠጅና የሚያሰክር መጠጥ አይጠጣም፤ ገናም በእናቱ ማኅፀን ሳለ መንፈስ ቅዱስ ይሞላበታል፤
12And Zacharias was troubled when he saw [him], and fear fell upon him.
16ከእስራኤልም ልጆች ብዙዎችን ወደ ጌታ ወደ አምላካቸው ይመልሳል።
13But the angel said unto him, Fear not, Zacharias: because thy supplication is heard, and thy wife Elisabeth shall bear thee a son, and thou shalt call his name John.
17እርሱም የተዘጋጁትን ሕዝብ ለጌታ እንዲያሰናዳ፥ የአባቶችን ልብ ወደ ልጆች የማይታዘዙትንም ወደ ጻድቃን ጥበብ ይመልስ ዘንድ በኤልያስ መንፈስና ኃይል በፊቱ ይሄዳል።
14And thou shalt have joy and gladness; and many shall rejoice at his birth.
18ዘካርያስም መልአኩን። እኔ ሽማግሌ ነኝ ምስቴም በዕድሜዋ አርጅታለችና ይህን በምን አውቃለሁ? አለው።
15For he shall be great in the sight of the Lord, and he shall drink no wine nor strong drink; and he shall be filled with the Holy Spirit, even from his mother's womb.
19መልአኩም መልሶ። እኔ በእግዚአብሔር ፊት የምቆመው ገብርኤል ነኝ፥ እንድናገርህም ይህችንም የምሥራች እንድሰብክልህ ተልኬ ነበር፤
16And many of the children of Israel shall be turn unto the Lord their God.
20እነሆም፥ በጊዜው የሚፈጸመውን ቃሌን ስላላመንህ፥ ይህ ነገር እስከሚሆን ቀን ድረስ ዲዳ ትሆናለህ መናገርም አትችልም አለው።
17And he shall go before his face in the spirit and power of Elijah, to turn the hearts of the fathers to the children, and the disobedient [to walk] in the wisdom of the just; to make ready for the Lord a people prepared [for him].
21ሕዝቡም ዘካርያስን ይጠብቁት ነበር፤ በቤተ መቅደስም ውስጥ ስለ ዘገየ ይደነቁ ነበር።
18And Zacharias said unto the angel, Whereby shall I know this? for I am an old man, and my wife well stricken in years.
22በወጣም ጊዜ ሊነግራቸው አልቻለም፥ በቤተ መቅደስም ራእይ እንዳየ አስተዋሉ፤ እርሱም ይጠቅሳቸው ነበር፤ ድዳም ሆኖ ኖረ።
19And the angel answering said unto him, I am Gabriel, that stand in the presence of God; and I was sent to speak unto thee, and to bring thee these good tidings.
23የማገልገሉም ወራት ሲፈጸም ወደ ቤቱ ሄደ።
20And behold, thou shalt be silent and not able to speak, until the day that these things shall come to pass, because thou believedst not my words, which shall be fulfilled in their season.
24ከዚህም ወራት በኋላ ሚስቱ ኤልሳቤጥ ፀነሰችና። ነቀፌታዬን ከሰው መካከል ያስወግድልኝ ዘንድ ጌታ በተመለከተበት ወራት እንዲህ አድርጎልኛል ስትል ራስዋን አምስት ወር ሰወረች።
21And the people were waiting for Zacharias, and they marvelled while he tarried in the temple.
26በስድስተኛውም ወር መልአኩ ገብርኤል ናዝሬት ወደምትባል ወደ ገሊላ ከተማ፥
22And when he came out, he could not speak unto them: and they perceived that he had seen a vision in the temple: and he continued making signs unto them, and remained dumb.
27ከዳዊት ወገን ለሆነው ዮሴፍ ለሚባል ሰው ወደ ታጨች ወደ አንዲት ድንግል ከእግዚአብሔር ዘንድ ተላከ፥ የድንግሊቱም ስም ማርያም ነበረ።
23And it came to pass, when the days of his ministration were fulfilled, he departed unto his house.
28መልአኩም ወደ እርስዋ ገብቶ። ደስ ይበልሽ፥ ጸጋ የሞላብሽ ሆይ፥ ጌታ ከአንቺ ጋር ነው፤ አንቺ ከሴቶች መካከል የተባረክሽ ነሽ አላት።
24And after these days Elisabeth his wife conceived; and she hid herself five months, saying,
29እርስዋም ባየችው ጊዜ ከንግግሩ በጣም ደነገጠችና። ይህ እንዴት ያለ ሰላምታ ነው? ብላ አሰበች።
25Thus hath the Lord done unto me in the days wherein he looked upon [me], to take away my reproach among men.
30መልአኩም እንዲህ አላት። ማርያም ሆይ፥ በእግዚአብሔር ፊት ጸጋ አግኝተሻልና አትፍሪ።
26Now in the sixth month the angel Gabriel was sent from God unto a city of Galilee, named Nazareth,
31እነሆም፥ ትፀንሻለሽ ወንድ ልጅም ትወልጃለሽ፥ ስሙንም ኢየሱስ ትዪዋለሽ።
27to a virgin betrothed to a man whose name was Joseph, of the house of David; and the virgin's name was Mary.
32እርሱ ታላቅ ይሆናል የልዑል ልጅም ይባላል፥ ጌታ አምላክም የአባቱን የዳዊትን ዙፋን ይሰጠዋል፤
28And he came in unto her, and said, Hail, thou that art highly favored, the Lord [is] with thee.
33በያዕቆብ ቤትም ላይ ለዘለላም ይነግሣል፥ ለመንግሥቱም መጨረሻ የለውም።
29But she was greatly troubled at the saying, and cast in her mind what manner of salutation this might be.
34ማርያምም መልአኩን። ወንድ ስለማላውቅ ይህ እንዴት ይሆናል? አለችው።
30And the angel said unto her, Fear not, Mary: for thou hast found favor with God.
35መልአኩም መልሶ እንዲህ አላት። መንፈስ ቅዱስ በአንቺ ላይ ይመጣል፥ የልዑልም ኃይል ይጸልልሻል ስለዚህ ደግሞ ከአንቺ የሚወለደው ቅዱስ የእግዚአብሔር ልጅ ይባላል።
31And behold, thou shalt conceive in thy womb, and bring forth a son, and shalt call his name JESUS.
36እነሆም ዘመድሽ ኤልሳቤጥ፥ እርስዋ ደግሞ በእርጅናዋ ወንድ ልጅ ፀንሳለች፥ ለእርስዋም መካን ትባል ለነበረችው ይህ ስድስተኛ ወር ነው፤
32He shall be great, and shall be called the Son of the Most High: and the Lord God shall give unto him the throne of his father David:
37ለእግዚአብሔር የሚሳነው ነገር የለምና።
33and he shall reign over the house of Jacob for ever; and of his kingdom there shall be no end.
38ማርያምም። እነሆኝ የጌታ ባሪያ እንደ ቃልህ ይሁንልኝ አለች። መልአኩም ከእርስዋ ሄደ።
34And Mary said unto the angel, How shall this be, seeing I know not a man?
39ማርያምም በዚያ ወራት ተነሥታ ወደ ተራራማው አገር ወደ ይሁዳ ከተማ ፈጥና ወጣች፥
35And the angel answered and said unto her, The Holy Spirit shall come upon thee, and the power of the Most High shall overshadow thee: wherefore also the holy thing which is begotten shall be called the Son of God.
40ወደ ዘካርያስም ቤት ገብታ ኤልሳቤጥን ተሳለመቻት።
36And behold, Elisabeth thy kinswoman, she also hath conceived a son in her old age; and this is the sixth month with her that was called barren.
41ኤልሳቤጥም የማርያምን ሰላምታ በሰማች ጊዜ ፅንሱ በማኅፀንዋ ውስጥ ዘለለ፤ በኤልሳቤጥም መንፈስ ቅዱስ ሞላባት፥
37For no word from God shall be void of power.
42በታላቅ ድምፅም ጮኻ እንዲህ አለች። አንቺ ከሴቶች መካከል የተባረክሽ ነሽ፥ የማኅፀንሽም ፍሬ የተባረከ ነው።
38And Mary said, Behold, the handmaid of the Lord; be it unto me according to thy word. And the angel departed from her.
43የጌታዬ እናት ወደ እኔ ትመጣ ዘንድ እንዴት ይሆንልኛል?
39And Mary arose in these days and went into the hill country with haste, into a city of Judah;
44እነሆ፥ የሰላምታሽ ድምጽ በጆሮዬ በመጣ ጊዜ ፅንሱ በማኅፀኔ በደስታ ዘሎአልና።
40and entered into the house of Zacharias and saluted Elisabeth.
45ከጌታ፤ የተነገረላት ቃል ይፈጸማልና ያመነች ብፅዕት ናት።
41And it came to pass, when Elisabeth heard the salutation of Mary, the babe leaped in her womb; and Elisabeth was filled with the Holy Spirit;
46ማርያምም እንዲህ አለች።
42and she lifted up her voice with a loud cry, and said, Blessed [art] thou among women, and blessed [is] the fruit of thy womb.
47ነፍሴ ጌታን ታከብረዋለች፥ መንፈሴም በአምላኬ በመድኃኒቴ ሐሴት ታደርጋለች፤
43And whence is this to me, that the mother of my Lord should come unto me?
48የባሪያይቱን ውርደት ተመልክቶአልና። እነሆም፥ ከዛሬ ጀምሮ ትውልድ ሁሉ ብፅዕት ይሉኛል፤
44For behold, when the voice of thy salutation came into mine ears, the babe leaped in my womb for joy.
49ብርቱ የሆነ እርሱ በእኔ ታላቅ ሥራ አድርጎአልና፤ ስሙም ቅዱስ ነው።
45And blessed [is] she that believed; for there shall be a fulfilment of the things which have been spoken to her from the Lord.
50ምሕረቱም ለሚፈሩት እስከ ትውልድና ትውልድ ይኖራል።
46And Mary said, My soul doth magnify the Lord,
51በክንዱ ኃይል አድርጎአል፤ ትዕቢተኞችን በልባቸው አሳብ በትኖአል፤
47And my spirit hath rejoiced in God my Saviour.
52ገዥዎችን ከዙፋናቸው አዋርዶአል፤ ትሑታንንም ከፍ አድርጎአል፤
48For he hath looked upon the low estate of his handmaid: For behold, from henceforth all generations shall call me blessed.
53የተራቡትን በበጎ ነገር አጥግቦአል፤ ባለ ጠጎችንም ባዶአቸውን ሰዶአቸዋል።
49For he that is mighty hath done to me great things; And holy is his name.
54ለአባቶቻችን እንደ ተናገረ፥ ለአብርሃምና ለዘሩ ለዘላለም ምሕረቱ ትዝ እያለው እስራኤልን ብላቴናውን ረድቶአል።
50And his mercy is unto generations and generations On them that fear him.
56ማርያምም ሦስት ወር የሚያህል በእርስዋ ዘንድ ተቀመጠች ወደ ቤትዋም ተመለሰች።
51He hath showed strength with his arm; He hath scattered the proud in the imagination of their heart.
57የኤልሳቤጥም የመውለጃዋ ጊዜ ደረሰ፥ ወንድ ልጅም ወለደች።
52He hath put down princes from [their] thrones, And hath exalted them of low degree.
58ጎረቤቶችዋም ዘመዶችዋም ጌታ ምሕረቱን እንዳገነነላት ሰምተው ከእርስዋ ጋር ደስ አላቸው።
53The hungry he hath filled with good things; And the rich he hath sent empty away.
59በስምንተኛውም ቀን ሕፃኑን ሊገርዙት መጡ፥ በአባቱም ስም ዘካርያስ ሊሉት ወደዱ።
54He hath given help to Israel his servant, That he might remember mercy
60እናቱ ግን መልሳ። አይሆንም፥ ዮሐንስ ይባል እንጂ አለች።
55(As he spake unto our fathers) Toward Abraham and his seed for ever.
61እነርሱም። ከወገንሽ ማንም በዚህ ስም የተጠራ የለም አሉአት።
56And Mary abode with her about three months, and returned unto her house.
62አባቱንም ማን ሊባል እንዲወድ ጠቀሱት።
57Now Elisabeth's time was fulfilled that she should be delivered; and she brought forth a son.
63ብራናም ለምኖ። ስሙ ዮሐንስ ነው ብሎ ጻፈ። ሁሉም አደነቁ።
58And her neighbors and her kinsfolk heard that the Lord had magnified his mercy towards her; and they rejoiced with her.
64ያንጊዜም አፉ ተከፈተ መላሱም ተፈታ እግዚአብሔርንም እየባረከ ተናገረ።
59And it came to pass on the eighth day, that they came to circumcise the child; and they would have called him Zacharias, after the name of the father.
65ለጎረቤቶቻቸውም ሁሉ ፍርሃት ሆነ፤ ይህም ሁሉ ነገር በይሁዳ በተራራማው አገር ሁሉ ተወራ፤
60And his mother answered and said, Not so; but he shall be called John.
66የሰሙትም ሁሉ። እንኪያ ይህ ሕፃን ምን ይሆን? እያሉ በልባቸው አኖሩት፤ የጌታ እጅ ከእርሱ ጋር ነበረችና።
61And they said unto her, There is none of thy kindred that is called by this name.
67አባቱ ዘካርያስም መንፈስ ቅዱስ ሞላበትና ትንቢት ተናገረ እንዲህም አለ።
62And they made signs to his father, what he would have him called.
68የእስራኤል ጌታ አምላክ ይባረክ፥ ጐብኝቶ ለሕዝቡ ቤዛ አድርጎአልና፤
63And he asked for a writing tablet, and wrote, saying, His name is John. And they marvelled all.
69ከጥንት ጀምሮ በነበሩት በቅዱሳን ነቢያት አፍ እንደ ተናገረ፥ በብላቴናው በዳዊት ቤት የመዳን ቀንድን አስነስቶልናል፤
64And his mouth was opened immediately, and his tongue [loosed], and he spake, blessing God.
71ማዳኑም ከወደረኞቻችንና ከሚጠሉን ሁሉ እጅ ነው፤
65And fear came on all that dwelt round about them: and all these sayings were noised abroad throughout all the hill country of Judaea.
72እንደዚህ ለአባቶቻችን ምሕረት አደረገ፤ ለአባታችን ለአብርሃምም የማለውን መሐላውን ቅዱሱን ኪዳን አሰበ፤
66And all that heard them laid them up in their heart, saying, What then shall this child be? For the hand of the Lord was with him.
74በእርሱም ከጠላቶቻችን እጅ ድነን በዘመናችን ሁሉ ያለ ፍርሃት በቅድስናና በጽድቅ በፊቱ እንድናገለግለው ሰጠን።
67And his father Zacharias was filled with the Holy Spirit, and prophesied, saying,
76ደግሞም አንተ ሕፃን ሆይ፥ የልዑል ነቢይ ትባላለህ፥ መንገዱን ልትጠርግ በጌታ ፊት ትሄዳለህና፤
68Blessed [be] the Lord, the God of Israel; For he hath visited and wrought redemption for his people,
77እንደዚህም የኃጢአታቸው ስርየት የሆነውን የመዳን እውቀት ለሕዝቡ ትሰጣለህ፤
69And hath raised up a horn of salvation for us In the house of his servant David
78ይህም ከላይ የመጣ ብርሃን በጐበኘበት በአምላካችን ምሕረትና ርኅራኄ ምክንያት ነው፤
70(As he spake by the mouth of his holy prophets that have been from of old),
79ብርሃኑም በጨለማና በሞት ጥላ ተቀምጠው ላሉት ያበራል እግሮቻችንንም በሰላም መንገድ ያቀናል።
71Salvation from our enemies, and from the hand of all that hate us;
80ሕፃኑም አደገ በመንፈስም ጠነከረ፥ ለእስራኤልም እስከ ታየበት ቀን ድረስ በምድረ በዳ ኖረ።
72To show mercy towards, our fathers, And to remember his holy covenant;
73The oath which he spake unto Abraham our father,
74To grant unto us that we being delivered out of the hand of our enemies Should serve him without fear,
75In holiness and righteousness before him all our days.
76Yea and thou, child, shalt be called the prophet of the Most High: For thou shalt go before the face of the Lord to make ready his ways;
77To give knowledge of salvation unto his people In the remission of their sins,
78Because of the tender mercy of our God, Whereby the dayspring from on high shall visit us,
79To shine upon them that sit in darkness and the shadow of death; To guide our feet into the way of peace.
80And the child grew, and waxed strong in spirit, and was in the deserts till the day of his showing unto Israel.