1ወዲያውም ማለዳ የካህናት አለቆች ከሽማግሌዎችና ከጻፎች ከሸንጎውም ሁሉ ጋር ከተማከሩ በኋላ፥ ኢየሱስን አሳስረው ወሰዱትና ለጲላጦስ አሳልፈው ሰጡት።
1And straightway in the morning the chief priests with the elders and scribes, and the whole council, held a consultation, and bound Jesus, and carried him away, and delivered him up to Pilate.
2ጲላጦስም። አንተ የአይሁድ ንጉሥ ነህን? ብሎ ጠየቀው። እርሱም። አንተ አልህ ብሎ መለሰለት።
2And Pilate asked him, Art thou the King of the Jews? And he answering saith unto him, Thou sayest.
3የካህናት አለቆችም ብዙ ያሳጡት ነበር፤ እርሱ ግን ምንም አልመለሰም።
3And the chief priests accused him of many things.
4ጲላጦስም ደግሞ። አንዳች አትመልስምን? እነሆ፥ በስንት ነገር ያሳጡሃል ብሎ ጠየቀው።
4And Pilate again asked him, saying, Answerest thou nothing? behold how many things they accuse thee of.
5ኢየሱስም ከዚያ በኋላ ጲላጦስ እስኪደነቅ ድረስ ምንም አልመለሰም።
5But Jesus no more answered anything; insomuch that Pilate marvelled.
6በዚያም በዓል የለመኑትን አንድ እስረኛ ይፈታላቸው ነበር።
6Now at the feast he used to release unto them one prisoner, whom they asked of him.
7በዓመፅም ነፍስ ከገደሉት ከዓመፀኞች ጋር የታሰረ በርባን የተባለ ነበረ።
7And there was one called Barabbas, [lying] bound with them that had made insurrection, men who in the insurrection had committed murder.
8ሕዝቡም ወጥተው እንደ ልማዱ ያደርግላቸው ዘንድ እየጮኹ ይለምኑት ጀመር።
8And the multitude went up and began to ask him [to do] as he was wont to do unto them.
9ጲላጦስም። የአይሁድን ንጉሥ እፈታላችሁ ዘንድ ትወዳላችሁን? ብሎ መለሰላቸው፤
9And Pilate answered them, saying, Will ye that I release unto you the King of the Jews?
10የካህናት አለቆች በቅንዓት አሳልፈው እንደ ሰጡት ያውቅ ነበርና።
10For he perceived that for envy the chief priests had delivered him up.
11የካህናት አለቆች ግን በርባንን በእርሱ ፈንታ ይፈታላቸው ዘንድ ሕዝቡን አወኩአቸው።
11But the chief priests stirred up the multitude, that he should rather release Barabbas unto them.
12ጲላጦስም ዳግመኛ መልሶ። እንግዲህ የአይሁድ ንጉሥ የምትሉትን ምን ላደርገው ትወዳላችሁ? አላቸው።
12And Pilate again answered and said unto them, What then shall I do unto him whom ye call the King of the Jews?
13እነርሱም ዳግመኛ። ስቀለው እያሉ ጮኹ።
13And they cried out again, Crucify him.
14ጲላጦስም። ምን ነው? ያደረገው ክፋት ምንድር ነው? አላቸው። እነርሱ ግን። ስቀለው እያሉ ጩኸት አበዙ።
14And Pilate said unto them, Why, what evil hath he done? But they cried out exceedingly, Crucify him.
15ጲላጦስም የሕዝቡን ፈቃድ ሊያደርግ ወዶ በርባንን ፈታላቸው፥ ኢየሱስንም ገርፎ እንዲሰቀል አሳልፎ ሰጠ።
15And Pilate, wishing to content the multitude, released unto them Barabbas, and delivered Jesus, when he had scourged him, to be crucified.
16ወታደሮችም ፕራይቶሪዮን ወደሚባል ግቢ ውስጥ ወሰዱት፥ ጭፍራውንም ሁሉ በአንድነት ጠሩ።
16And the soldiers led him away within the court, which is the Praetorium; and they call together the whole band.
17ቀይ ልብስም አለበሱት፥ የእሾህ አክሊልም ጎንጉነው ደፉበት፤
17And they clothe him with purple, and platting a crown of thorns, they put it on him;
18የአይሁድ ንጉሥ ሆይ፥ ሰላም ለአንተ ይሁን እያሉ እጅ ይነሱት ጀመር፤
18and they began to salute him, Hail, King of the Jews!
19ራሱንም በመቃ መቱት ተፉበትም፥ ተንበርክከውም ሰገዱለት።
19And they smote his head with a reed, and spat upon him, and bowing their knees worshipped him.
20ከተዘባበቱበትም በኋላ ቀዩን ልብስ ገፈፉት፥ ልብሱንም አለበሱት፥ ሊሰቅሉትም ወሰዱት።
20And when they had mocked him, they took off from him the purple, and put on him his garments. And they lead him out to crucify him.
21አንድ መንገድ አላፊም የአሌክስንድሮስና የሩፎስ አባት ስምዖን የተባለ የቀሬና ሰው ከገጠር ሲመጣ መስቀሉን ይሸከም ዘንድ አስገደዱት።
21And they compel one passing by, Simon of Cyrene, coming from the country, the father of Alexander and Rufus, to go [with them], that he might bear his cross.
22ትርጓሜውም የራስ ቅል ስፍራ ወደሚሆን ጎልጎታ ወደተባለ ስፍራ ወሰዱት።
22And they bring him unto the place Golgotha, which is, being interpreted, The place of a skull.
23ከርቤም የተቀላቀለበትን የወይን ጠጅ እንዲጠጣ ሰጡት፤ እርሱ ግን አልተቀበለም።
23And they offered him wine mingled with myrrh: but he received it not.
24ሰቀሉትም፥ ልብሱንም ማን ማን እንዲወስድ ዕጣ ተጣጥለው ተካፈሉ።
24And they crucify him, and part his garments among them, casting lots upon them, what each should take.
25በሰቀሉትም ጊዜ ሦስት ሰዓት ነበረ።
25And it was the third hour, and they crucified him.
26የክሱ ጽሕፈትም። የአይሁድ ንጉሥ የሚል ተጽፎ ነበር።
26And the superscription of his accusation was written over, THE KING OF THE JEWS.
27ከእርሱም ጋር ሁለት ወንበዶች አንዱን በቀኙ አንዱንም በግራው ሰቀሉ።
27And with him they crucify two robbers; one on his right hand, and one on his left.
28መጽሐፍም። ከአመፀኞች ጋር ተቆጠረ ያለው ተፈጸመ።
28[And the scripture was fulfilled, which saith, And he was reckoned with transgressors.]
29የሚያልፉትም ራሳቸውን እየነቀነቁ ይሰድቡት ነበርና። ዋ፥ ቤተ መቅደስን የምታፈርስ በሦስት ቀንም የምትሠራ፥
29And they that passed by railed on him, wagging their heads, and saying, Ha! Thou that destroyest the temple, and buildest it in three days,
30ከመስቀል ወርደህ ራስህን አድን አሉ።
30save thyself, and come down from the cross.
31እንዲሁም የካህናት አለቆች ደግሞ ከጻፎች ጋር እርስ በርሳቸው እየተዘባበቱ። ሌሎችን አዳነ፤ ራሱን ሊያድን አይችልም፤
31In like manner also the chief priests mocking [him] among themselves with the scribes said, He saved others; himself he cannot save.
32አይተን እናምን ዘንድ የእስራኤል ንጉሥ ክርስቶስ አሁን ከመስቀል ይውረድ አሉ። ከእርሱም ጋር የተሰቀሉት ይነቅፉት ነበር።
32Let the Christ, the King of Israel, now come down from the cross, that we may see and believe. And they that were crucified with him reproached him.
33ስድስት ሰዓትም በሆነ ጊዜ፥ እስከ ዘጠኝ ሰዓት በምድር ሁሉ ላይ ጨለማ ሆነ።
33And when the sixth hour was come, there was darkness over the whole land until the ninth hour.
34በዘጠኝ ሰዓትም ኢየሱስ። ኤሎሄ፥ ኤሎሄ፥ ላማ ሰበቅታኒ? ብሎ በታላቅ ድምፅ ጮኸ፤ ትርጓሜውም አምላኬ፥ አምላኬ፥ ለምን ተውኸኝ? ማለት ነው።
34And at the ninth hour Jesus cried with a loud voice, Eloi, Eloi, lama sabachthani? which is, being interpreted, My God, my God, why hast thou forsaken me?
35በዚያም ከቆሙት ሰዎች ሰምተው። እነሆ፥ ኤልያስን ይጠራል አሉ።
35And some of them that stood by, when they heard it, said, Behold, he calleth Elijah.
36አንዱም ሮጦ ሆምጣጤ በሰፍነግ ሞላ በመቃም አድርጎ። ተዉ፤ ኤልያስ ሊያወርደው ይመጣ እንደ ሆነ እንይ እያለ አጠጣው።
36And one ran, and filling a sponge full of vinegar, put it on a reed, and gave him to drink, saying, Let be; let us see whether Elijah cometh to take him down.
37ኢየሱስም በታላቅ ድምፅ ጮኸ ነፍሱንም ሰጠ።
37And Jesus uttered a loud voice, and gave up the ghost.
38የቤተ መቅደስም መጋረጃ ከላይ እስከ ታች ከሁለት ተቀደደ።
38And the veil of the temple was rent in two from the top to the bottom.
39በዚያም በአንጻሩ የቆመ የመቶ አለቃ እንደዚህ ጮኾ ነፍሱን እንደ ሰጠ ባየ ጊዜ። ይህ ሰው በእውነት የእግዚአብሔር ልጅ ነበረ አለ።
39And when the centurion, who stood by over against him, saw that he so gave up the ghost, he said, Truly this man was the Son of God.
40ሴቶችም ደግሞ በሩቅ ሆነው ይመለከቱ ነበር፤ ከእነርሱም በገሊላ ሳለ ይከተሉትና ያገለግሉት የነበሩ መግደላዊት ማርያም የታናሹ ያዕቆብና የዮሳም እናት ማርያም ሰሎሜም ነበሩ፥ ከእርሱም ጋር ወደ ኢየሩሳሌም የወጡ ሌሎች ብዙዎች ሴቶች ነበሩ።
40And there were also women beholding from afar: among whom [were] both Mary Magdalene, and Mary the mother of James the less and of Joses, and Salome;
42አሁንም በመሸ ጊዜ የሰንበት ዋዜማ የሆነ የማዘጋጀት ቀን ስለ ነበረ፥ የከበረ አማካሪ የሆነ የአርማትያስ ዮሴፍ መጣ፥
41who, when he was in Galilee, followed him, and ministered unto him; and many other women that came up with him unto Jerusalem.
43እርሱም ደግሞ የእግዚአብሔርን መንግሥት ይጠባበቅ ነበር፤ ደፍሮም ወደ ጲላጦስ ገባና የኢየሱስን ሥጋ ለመነው።
42And when even was now come, because it was the Preparation, that is, the day before the sabbath,
44ጲላጦስም አሁኑን እንዴት ሞተ ብሎ ተደነቀ፥ የመቶ አለቃውንም ጠርቶ ከሞተ ቆይቶአልን? ብሎ ጠየቀው፤
43there came Joseph of Arimathaea, a councillor of honorable estate, who also himself was looking for the kingdom of God; and he boldly went in unto Pilate, and asked for the body of Jesus.
45ከመቶ አለቃውም ተረድቶ በድኑን ለዮሴፍ ሰጠው።
44And Pilate marvelled if he were already dead: and calling unto him the centurion, he asked him whether he had been any while dead.
46በፍታም ገዝቶ አውርዶም በበፍታ ከፈነው ከዓለትም በተወቀረ መቃብር አኖረው፥ በመቃብሩ ደጃፍም ድንጋይ አንከባለለ።
45And when he learned it of the centurion, he granted the corpse to Joseph.
47መግደላዊትም ማርያም የዮሳም እናት ማርያም ወዴት እንዳኖሩት ይመለከቱ ነበር።
46And he bought a linen cloth, and taking him down, wound him in the linen cloth, and laid him in a tomb which had been hewn out of a rock; and he rolled a stone against the door of the tomb.
47And Mary Magdalene and Mary the [mother] of Joses beheld where he was laid.