1ወንድሞች ሆይ፥ የልቤ በጎ ፈቃድና ስለ እስራኤል ወደ እግዚአብሔር ልመናዬ እንዲድኑ ነው።
1Brethren, my heart's desire and my supplication to God is for them, that they may be saved.
2በእውቀት አይቅኑ እንጂ ለእግዚአብሔር እንዲቀኑ እመሰክርላቸዋለሁና።
2For I bear them witness that they have a zeal for God, but not according to knowledge.
3የእግዚአብሔርን ጽድቅ ሳያውቁ የራሳቸውንም ጽድቅ ሊያቆሙ ሲፈልጉ፥ ለእግዚአብሔር ጽድቅ አልተገዙም።
3For being ignorant of God's righteousness, and seeking to establish their own, they did not subject themselves to the righteousness of God.
4የሚያምኑ ሁሉ ይጸድቁ ዘንድ ክርስቶስ የሕግ ፍጻሜ ነውና።
4For Christ is the end of the law unto righteousness to every one that believeth.
5ሙሴ ከሕግ የሆነውን ጽድቅ የሚያደርገው ሰው በእርሱ በሕይወት እንዲኖር ጽፎአልና።
5For Moses writeth that the man that doeth the righteousness which is of the law shall live thereby.
6ከእምነት የሆነ ጽድቅ ግን እንዲህ ይላል። በልብህ። ማን ወደ ሰማይ ይወጣል? አትበል፤ ይህ ክርስቶስን ለማውረድ ነው፤
6But the righteousness which is of faith saith thus, Say not in thy heart, Who shall ascend into heaven? (that is, to bring Christ down:)
7ወይም። በልብህ። ወደ ጥልቁ ማን ይወርዳል? አትበል፤ ይህ ክርስቶስን ከሙታን ለማውጣት ነው።
7or, Who shall descend into the abyss? (That is, to bring Christ up from the dead.)
8ነገር ግን ምን ይላል? በአፍህ በልብህም ሆኖ ቃሉ ቀርቦልሃል፤ ይህም የምንሰብከው የእምነት ቃል ነው።
8But what saith it? The word is nigh thee, in thy mouth, and in thy heart: that is, the word of faith, which we preach:
9ኢየሱስ ጌታ እንደ ሆነ በአፍህ ብትመሰክር እግዚአብሔርም ከሙታን እንዳስነሣው በልብህ ብታምን ትድናለህና፤
9because if thou shalt confess with thy mouth Jesus [as] Lord, and shalt believe in thy heart that God raised him from the dead, thou shalt be saved:
10ሰው በልቡ አምኖ ይጸድቃልና በአፉም መስክሮ ይድናልና።
10for with the heart man believeth unto righteousness; and with the mouth confession is made unto salvation.
11መጽሐፍ። በእርሱ የሚያምን ሁሉ አያፍርም ይላልና።
11For the scripture saith, Whosoever believeth on him shall not be put to shame.
12በአይሁዳዊና በግሪክ ሰው መካከል ልዩነት የለምና፤ አንዱ ጌታ የሁሉ ጌታ ነውና፥ ለሚጠሩትም ሁሉ ባለ ጠጋ ነው፤
12For there is no distinction between Jew and Greek: for the same [Lord] is Lord of all, and is rich unto all that call upon him:
13የጌታን ስም የሚጠራ ሁሉ ይድናልና።
13for, Whosoever shall call upon the name of the Lord shall be saved.
14እንግዲህ ያላመኑበትን እንዴት አድርገው ይጠሩታል? ባልሰሙትስ እንዴት ያምናሉ? ያለ ሰባኪስ እንዴት ይሰማሉ?
14How then shall they call on him in whom they have not believed? and how shall they believe in him whom they have not heard? and how shall they hear without a preacher?
15መልካሙን የምሥራች የሚያወሩ እግሮቻቸው እንዴት ያማሩ ናቸው ተብሎ እንደ ተጻፈ ካልተላኩ እንዴት ይሰብካሉ?
15and how shall they preach, except they be sent? even as it is written, How beautiful are the feet of them that bring glad tidings of good things!
16ነገር ግን ሁሉ ለምሥራቹ ቃል አልታዘዙም። ኢሳይያስ። ጌታ ሆይ፥ ምስክርነታችንን ማን አመነ? ብሎአልና።
16But they did not all hearken to the glad tidings. For Isaiah saith, Lord, who hath believed our report?
17እንግዲያስ እምነት ከመስማት ነው መስማትም በእግዚአብሔር ቃል ነው።
17So belief [cometh] of hearing, and hearing by the word of Christ.
18ዳሩ ግን። ባይሰሙ ነው ወይ? እላለሁ። በእውነት። ድምፃቸው በምድር ሁሉ ላይ ቃላቸውም እስከ ዓለም ዳርቻ ወጣ።
18But I say, Did they not hear? Yea, verily, Their sound went out into all the earth, And their words unto the ends of the world.
19ነገር ግን። እስራኤል ባያውቁ ነው ወይ? እላለሁ። ሙሴ አስቀድሞ። እኔ ሕዝብ በማይሆነው አስቀናችኋለሁ በማያስተውልም ሕዝብ አስቆጣችኋለሁ
19But I say, Did Israel not know? First Moses saith, I will provoke you to jealousy with that which is no nation, With a nation void of understanding will I anger you.
20ብሎአል። ኢሳይያስም ደፍሮ። ላልፈለጉኝ ተገኘሁ፥ ላልጠየቁኝም ተገለጥሁ አለ።
20And Isaiah is very bold, and saith, I was found of them that sought me not; I became manifest unto them that asked not of me.
21ስለ እስራኤል ግን። ቀኑን ሁሉ ወደማይታዘዝና ወደሚቃወም ሕዝብ እጆቼን ዘረጋሁ ይላል።
21But as to Israel he saith, All the day long did I spread out my hands unto a disobedient and gainsaying people.