Amharic: New Testament

Darby's Translation

1 Corinthians

11

1እኔ ክርስቶስን እንደምመስል እኔን ምሰሉ።
1Be my imitators, even as *I* also [am] of Christ.
2ወንድሞች ሆይ፥ በሁሉ ስለምታስቡኝና አሳልፌ እንደ ሰጠኋችሁ ወግን ፈጽማችሁ ስለ ያዛችሁ አመሰግናችኋለሁ።
2Now I praise you, that in all things ye are mindful of me; and that as I have directed you, ye keep the directions.
3ነገር ግን የወንድ ሁሉ ራስ ክርስቶስ፥ የሴትም ራስ ወንድ፥ የክርስቶስም ራስ እግዚአብሔር እንደ ሆነ ልታውቁ እወዳለሁ።
3But I wish you to know that the Christ is the head of every man, but woman's head [is] the man, and the Christ's head God.
4ራሱን ተከናንቦ የሚጸልይ ወይም ትንቢት የሚናገር ወንድ ሁሉ ራሱን ያዋርዳል።
4Every man praying or prophesying, having [anything] on his head, puts his head to shame.
5ራስዋን ሳትሸፍን ግን የምትጸልይ ወይም ትንቢት የምትናገር ሴት ሁሉ ራስዋን ታዋርዳለች፤ እንደ ተላጨች ያህል አንድ ነውና።
5But every woman praying or prophesying with her head uncovered puts her own head to shame; for it is one and the same as a shaved [woman].
6ሴትም ራስዋን ባትሸፍን ጠጉርዋን ደግሞ ትቆረጥ፤ ለሴት ግን ጠጉርዋን መቆረጥ ወይም መላጨት የሚያሳፍር ከሆነ ራስዋን ትሸፍን።
6For if a woman be not covered, let her hair also be cut off. But if [it be] shameful to a woman to have her hair cut off or to be shaved, let her be covered.
7ወንድ የእግዚአብሔር ምሳሌና ክብር ስለ ሆነ ራሱን መከናነብ አይገባውም፤ ሴት ግን የወንድ ክብር ናት።
7For man indeed ought not to have his head covered, being God's image and glory; but woman is man's glory.
8ሴት ከወንድ ናት እንጂ ወንድ ከሴት አይደለምና።
8For man is not of woman, but woman of man.
9ሴት ስለ ወንድ ተፈጠረች እንጂ ወንድ ስለ ሴት አልተፈጠረምና።
9For also man was not created for the sake of the woman, but woman for the sake of the man.
10ስለዚህ ሴት ከመላእክት የተነሣ በራስዋ ሥልጣን ሊኖራት ይገባል።
10Therefore ought the woman to have authority on her head, on account of the angels.
11ነገር ግን በጌታ ዘንድ ሴት ያለ ወንድ ወንድም ያለ ሴት አይሆንም።
11However, neither [is] woman without man, nor man without woman, in [the] Lord.
12ሴት ከወንድ እንደ ሆነች እንዲሁ ወንድ ደግሞ በሴት ነውና፤ ሁሉም ከእግዚአብሔር ነው።
12For as the woman [is] of the man, so also [is] the man by the woman, but all things of God.
13በእናንተ በራሳችሁ መካከል ፍረዱ፤ ሴት ራስዋን ሳትሸፍን ወደ እግዚአብሔር ልትጸልይ ይገባታልን?
13Judge in yourselves: is it comely that a woman should pray to God uncovered?
14ወንድ ጠጉሩን ቢያስረዝም ነውር እንዲሆንበት፥ ሴት ግን ጠጉርዋን ብታስረዝም ክብር እንዲሆንላት ተፈጥሮ እንኳ አያስተምራችሁምን? ጠጉርዋ መጎናጸፊያ ሊሆን ተሰጥቶአታልና።
14Does not even nature itself teach you, that man, if he have long hair, it is a dishonour to him?
16ዳሩ ግን ማንም ሊከራከር ቢፈቅድ፥ እኛ ወይም የእግዚአብሔር አብያተ ክርስቲያናት እንዲህ ያለ ልማድ የለንም።
15But woman, if she have long hair, [it is] glory to her; for the long hair is given [to her] in lieu of a veil.
17ነገር ግን በምትሰበሰቡበት ጊዜ ለሚከፋ እንጂ ለሚሻል ስላልሆነ ይህን ትእዛዝ ስሰጥ የማመሰግናችሁ አይደለም።
16But if any one think to be contentious, *we* have no such custom, nor the assemblies of God.
18በመጀመሪያ ወደ ማኅበር ስትሰበሰቡ በመካከላችሁ መለያየት እንዳለ እሰማለሁና፥ በአንድ በኩልም አምናለሁ።
17But [in] prescribing [to you on] this [which I now enter on], I do not praise, [namely,] that ye come together, not for the better, but for the worse.
19በእናንተ ዘንድ የተፈተኑት እንዲገለጡ በመካከላችሁ ወገኖች ደግሞ ሊሆኑ ግድ ነውና።
18For first, when ye come together in assembly, I hear there exist divisions among you, and I partly give credit [to it].
20እንግዲህ አብራችሁ ስትሰበሰቡ የምትበሉት የጌታ እራት አይደለም፤
19For there must also be sects among you, that the approved may become manifest among you.
21በመብላት ጊዜ እያንዳንዱ የራሱን እራት ይበላልና፥ አንዱም ይራባል አንዱ ግን ይሰክራል።
20When ye come therefore together into one place, it is not to eat [the] Lord's supper.
22የምትበሉባቸውና የምትጠጡባቸው ቤቶች የላችሁምን? ወይስ የእግዚአብሔርን ማኅበር ትንቃላችሁን አንዳችም የሌላቸውን ታሳፍራላችሁን? ምን ልበላችሁ? በዚህ ነገር ላመስግናችሁን? አላመሰግናችሁም።
21For each one in eating takes his *own* supper before [others], and one is hungry and another drinks to excess.
23ለእናንተ ደግሞ አሳልፌ የሰጠሁትን እኔ ከጌታ ተቀብያለሁና፤
22Have ye not then houses for eating and drinking? or do ye despise the assembly of God, and put to shame them who have not? What shall I say to you? shall I praise you? In this [point] I do not praise.
24ጌታ ኢየሱስ አልፎ በተሰጠበት በዚያች ሌሊት እንጀራን አንሥቶ አመሰገነ፥ ቆርሶም። እንካችሁ ብሉ፤ ይህ ስለ እናንተ የሚሆን ሥጋዬ ነው፤ ይህን ለመታሰቢያዬ አድርጉት አለ።
23For *I* received from the Lord, that which I also delivered to you, that the Lord Jesus, in the night in which he was delivered up, took bread,
25እንደዚሁም ከእራት በኋላ ጽዋውን ደግሞ አንሥቶ። ይህ ጽዋ በደሜ የሚሆን አዲስ ኪዳን ነው፤ በጠጣችሁት ጊዜ ሁሉ ይህን ለመታሰቢያዬ አድርጉት አለ።
24and having given thanks broke [it], and said, This is my body, which [is] for you: this do in remembrance of me.
26ይህን እንጀራ በበላችሁ ጊዜ ሁሉ፥ ይህንም ጽዋ በጠጣችሁ ጊዜ ሁሉ ጌታ እስኪመጣ ድረስ ሞቱን ትናገራላችሁና።
25In like manner also the cup, after having supped, saying, This cup is the new covenant in my blood: this do, as often as ye shall drink [it], in remembrance of me.
27ስለዚህ ሳይገባው ይህን እንጀራ የበላ ወይም የጌታን ጽዋ የጠጣ ሁሉ የጌታ ሥጋና ደም ዕዳ አለበት።
26For as often as ye shall eat this bread, and drink the cup, ye announce the death of the Lord, until he come.
28ሰው ግን ራሱን ይፈትን፥ እንዲሁም ከእንጀራው ይብላ ከጽዋውም ይጠጣ፤
27So that whosoever shall eat the bread, or drink the cup of the Lord, unworthily, shall be guilty in respect of the body and of the blood of the Lord.
29ሳይገባው የሚበላና የሚጠጣ የጌታን ሥጋ ስለማይለይ ለራሱ ፍርድ ይበላልና፥ ይጠጣልምና።
28But let a man prove himself, and thus eat of the bread, and drink of the cup.
30ስለዚህ በእናንተ ዘንድ የደከሙና የታመሙ ብዙዎች አሉ አያሌዎችም አንቀላፍተዋል።
29For [the] eater and drinker eats and drinks judgment to himself, not distinguishing the body.
31ራሳችንን ብንመረምር ግን ባልተፈረደብንም ነበር፤
30On this account many among you [are] weak and infirm, and a good many are fallen asleep.
32ነገር ግን በተፈረደብን ጊዜ ከዓለም ጋር እንዳንኮነን በጌታ እንገሠጻለን።
31But if we judged ourselves, so were we not judged.
33ስለዚህ፥ ወንድሞቼ ሆይ፥ ለመብላት በተሰበሰባችሁ ጊዜ እርስ በርሳችሁ ተጠባበቁ።
32But being judged, we are disciplined of [the] Lord, that we may not be condemned with the world.
34ማንም የራበው ቢኖር ለፍርድ እንዳትሰበሰቡ በቤቱ ይብላ። የቀረውንም ነገር በመጣሁ ጊዜ እደነግጋለሁ።
33So that, my brethren, when ye come together to eat, wait for one another.
34If any one be hungry, let him eat at home, that ye may not come together for judgment. But the other things, whenever I come, I will set in order.