1ለቅዱሳንም ገንዘብን ስለ ማዋጣት፥ ለገላትያ አብያተ ክርስቲያናት እንደ ደነገግሁት እናንተ ደግሞ እንዲሁ አድርጉ።
1Now concerning the collection for the saints, as I directed the assemblies of Galatia, so do *ye* do also.
2እኔ ስመጣ ይህ የገንዘብ ማዋጣት ያን ጊዜ እንዳይሆን፥ ከእናንተ እያንዳንዱ በየሳምንቱ በፊተኛው ቀን እንደ ቀናው መጠን እያስቀረ በቤቱ ያስቀምጥ።
2On [the] first of [the] week let each of you put by at home, laying up [in] whatever [degree] he may have prospered, that there may be no collections when I come.
3ስመጣም ማናቸውም ቢሆኑ የታመኑ የሚመስሉአችሁ ሰዎች ቸርነታችሁን ወደ ኢየሩሳሌም ያደርሱ ዘንድ ደብዳቤ ሰጥቼ እልካቸዋለሁ፤
3And when I am arrived, whomsoever ye shall approve, these I will send with letters to carry your bounty to Jerusalem:
4እኔ ደግሞ ልሄድ የሚገባኝ ብሆን ከእኔ ጋር አብረው ይሄዳሉ።
4and if it be suitable that *I* also should go, they shall go with me.
5በመቄዶንያም ሳልፍ ወደ እናንተ እመጣለሁ፤ በመቄዶንያ አድርጌ አልፋለሁና፤
5But I will come to you when I shall have gone through Macedonia; for I do go through Macedonia.
6እናንተም ወደምሄድበት ወደ ማናቸውም ስፍራ በጉዞዬ እንድትረዱኝ ምናልባት በእናንተ ዘንድ እቆይ ወይም እከርም ይሆናል።
6But perhaps I will stay with you, or even winter with you, that *ye* may set me forward wheresoever I may go.
7አሁን እግረ መንገዴን ሳልፍ ልጎበኛችሁ አልወድምና፤ ጌታ ቢፈቅደው የሆነውን ዘመን በእናንተ ዘንድ ልሰነብት ተስፋ አደርጋለሁና።
7For I will not see you now in passing, for I hope to remain a certain time with you, if the Lord permit.
8በኤፌሶን ግን እስከ በዓለ ኀምሳ ድረስ እሰነብታለሁ።
8But I remain in Ephesus until Pentecost.
9ሥራ የሞላበት ትልቅ በር ተከፍቶልኛልና ተቃዋሚዎችም ብዙ ናቸው።
9For a great door is opened to me and an effectual [one], and [the] adversaries many.
10ጢሞቴዎስም የመጣ እንደ ሆነ በእናንተ ዘንድ ያለ ፍርሃት እንዲኖር ተጠንቀቁ፤ እንደ እኔ ደግሞ የጌታን ሥራ ይሠራልና፤ እንግዲህ ማንም አይናቀው።
10Now if Timotheus come, see that he may be with you without fear; for he works the work of the Lord, even as I.
11ነገር ግን ከወንድሞቹ ጋር እጠብቀዋለሁና ወደ እኔ ይመጣ ዘንድ በሰላም በጉዞው እርዱት።
11Let not therefore any one despise him; but set him forward in peace, that he may come to me; for I expect him with the brethren.
12ስለ ወንድማችን ስለ አጵሎስ ግን ከወንድሞቹ ጋር ወደ እናንተ ሊሄድ እጅግ አድርጌ ለምኜው ነበር፤ ዛሬም ለመምጣት ከቶ ፈቃድ አልነበረውም፥ ሲመቸው ግን ይመጣል።
12Now concerning the brother Apollos, I begged him much that he would go to you with the brethren; but it was not at all [his] will to go now; but he will come when he shall have good opportunity.
13ንቁ፥ በሃይማኖት ቁሙ፥ ጎልምሱ ጠንክሩ።
13Be vigilant; stand fast in the faith; quit yourselves like men; be strong.
14በእናንተ ዘንድ ሁሉ በፍቅር ይሁን።
14Let all things ye do be done in love.
15ወንድሞች ሆይ፥ የእስጢፋኖስ ቤተ ሰዎች የአካይያ በኩራት እንደ ሆኑ ቅዱሳንንም ለማገልገል ራሳቸውን እንደ ሰጡ ታውቃላችሁ፤
15But I beseech you, brethren, (ye know the house of Stephanas, that it is the first-fruits of Achaia, and they have devoted themselves to the saints for service,)
16እንደ እነርሱ ላሉትና አብሮ ለሚሠራ ለሚደክምም ሁሉ እናንተም እንድትገዙ እለምናችኋለሁ።
16that *ye* should also be subject to such, and to every one joined in the work and labouring.
17በእስጢፋኖስና በፈርዶናጥስ በአካይቆስም መምጣት ደስ ይለኛል፥ እናንተ ስለሌላችሁ የጎደለኝን ፈጽመዋልና፤ መንፈሴንና መንፈሳችሁን አሳርፈዋልና።
17But I rejoice in the coming of Stephanas and Fortunatus and Achaicus; because *they* have supplied what was lacking on your part.
18እንግዲህ እንደነዚህ ያሉትን እወቁአቸው።
18For they have refreshed my spirit and yours: own therefore such.
19የእስያ አብያተ ክርስቲያናት ሰላምታ ያቀርቡላችኋል። አቂላና ጵርስቅላ በቤታቸው ካለች ቤተ ክርስቲያን ጋር በጌታ እጅግ ሰላምታ ያቀርቡላችኋል።
19The assemblies of Asia salute you. Aquila and Priscilla, with the assembly in their house, salute you much in [the] Lord.
20ወንድሞች ሁሉ ሰላምታ ያቀርቡላችኋል። በተቀደሰ አሳሳም እርስ በርሳችሁ ሰላምታ ተሰጣጡ።
20All the brethren salute you. Salute one another with a holy kiss.
21እኔ ጳውሎስ ይህን ሰላምታ በገዛ እጄ ጽፌአለሁ።
21The salutation of [me] Paul with my own hand.
22ጌታን ኢየሱስ ክርስቶስን የማይወድ ቢኖር የተረገመ ይሁን። ጌታችን ሆይ፥ ና።
22If any one love not the Lord [Jesus Christ] let him be Anathema Maranatha.
23የጌታ የኢየሱስ ክርስቶስ ጸጋ ከእናንተ ጋር ይሁን።
23The grace of the Lord Jesus Christ [be] with you.
24ፍቅሬ በክርስቶስ ኢየሱስ ከሁላችሁ ጋር ነው። አሜን።
24My love [be] with you all in Christ Jesus. Amen.