Amharic: New Testament

Darby's Translation

1 Corinthians

9

1እኔ ነጻ አይደለሁምን? ሐዋርያስ አይደለሁምን? ጌታችንን ኢየሱስ ክርስቶስንስ አላየሁትምን? እናንተስ በጌታ ሥራዬ አይደላችሁምን?
1Am I not free? am I not an apostle? have I not seen Jesus our Lord? are not *ye* my work in [the] Lord?
2የሐዋርያነቴ ማኅተም በጌታ እናንተ ናችሁና ለሌሎች ሐዋርያ ባልሆን ለእናንተስ ምንም ቢሆን ሐዋርያ ነኝ።
2If I am not an apostle to others, yet at any rate I am to you: for the seal of mine apostleship are *ye* in [the] Lord.
3ለሚመረምሩኝ መልሴ ይህ ነው። ልንበላና ልንጠጣ መብት የለንምን?
3My defence to those who examine me is this:
5እንደ ሌሎቹ ሐዋርያትና እንደ ጌታ ወንድሞች እንደ ኬፋም፥ እኅት ሚስታችንን ይዘን ልንዞር መብት የለንምን?
4Have we not a right to eat and to drink?
6ወይስ ሥራን ለመተው መብት የሌለን እኔና በርናባስ ብቻ ነን?
5have we not a right to take round a sister [as] wife, as also the other apostles, and the brethren of the Lord, and Cephas?
7ከቶ በገዛ ገንዘቡ በወታደርነት የሚያገለግል ማን ነው? ወይስ ወይን ተክሎ ፍሬውን የማይበላ ማን ነው? ወይስ መንጋ እየጠበቀ ከመንጋው ወተት የማይጠጣ ማን ነው?
6Or *I* alone and Barnabas, have we not a right not to work?
8ይህን በሰው ሥልጣን ብቻ እላለሁን?
7Who ever carries on war at his own charges? who plants a vineyard and does not eat of its fruit? or who herds a flock and does not eat of the milk of the flock?
9ሕግስ ደግሞ ያን አይልምን? የሚያበራየውን በሬ አፉን አትሰር ተብሎ በሙሴ ሕግ ተጽፎአልና። እግዚአብሔርስ ስለ በሬዎች ይገደዋልን?
8Do I speak these things as a man, or does not the law also say these things?
10ይህን የሚለው ፈጽሞ ስለ እኛ አይደለምን? የሚያርስ በተስፋ ሊያርስ የሚያበራይም እንዲካፈል በተስፋ ሊያበራይ ስለሚገባው በእውነት ስለ እኛ ተጽፎአል።
9For in the law of Moses it is written, Thou shalt not muzzle the ox that is treading out corn. Is God occupied about the oxen,
11እኛ መንፈሳዊን ነገር የዘራንላችሁ ከሆንን የእናንተን የሥጋዊን ነገር እኛ ብናጭድ ትልቅ ነገር ነውን?
10or does he say [it] altogether for our sakes? For for our sakes it has been written, that the plougher should plough in hope, and he that treads out corn, in hope of partaking of [it].
12ሌሎች በእናንተ ላይ ይህን መብት የሚካፈሉ ከሆኑ እኛማ ይልቁን እንዴታ? ነገር ግን የክርስቶስን ወንጌል እንዳንከለክል በሁሉ እንታገሣለን እንጂ በዚህ መብት አልተጠቀምንም።
11If we have sown to you spiritual things, [is it a] great [thing] if *we* shall reap your carnal things?
13በመቅደስ ነገር የሚያገለግሉ ከመቅደስ የሆነውን ነገርን እንዲመገቡ፥ በመሠዊያውም የሚጸኑ ከመሠዊያው እንዲካፈሉ አታውቁምን?
12If others partake of this right over you, should not rather *we*? But we have not used this right, but we bear all things, that we may put no hindrance in the way of the glad tidings of the Christ.
14እንዲሁ ደግሞ ወንጌልን የሚሰብኩ ከወንጌል ቀለብ እንዲቀበሉ ጌታ ደንግጎአል።
13Do ye not know that they who labour [at] sacred things eat of the [offerings offered in the] temple; they that attend at the altar partake with the altar?
15እኔ ግን ከእነዚህ ሁሉ ምንም አልተጠቀምሁም። እንዲህ እንዲሆንልኝ ይህን አልጽፍም፤ ማንም ትምክህቴን ከንቱ ከሚያደርግብኝ ሞት ይሻለኛልና።
14So also the Lord has ordained to those that announce the glad tidings to live of the glad tidings.
16ወንጌልን ብሰብክ እንኳ የምመካበት የለኝም፤ ግድ ደርሶብኝ ነውና፤ ወንጌልንም ባልሰብክ ወዮልኝ።
15But *I* have used none of these things. Now I have not written these things that it should be thus in my case; for [it were] good for me rather to die than that any one should make vain my boast.
17ይህን በፈቃዴ ባደርገው ደመወዝ አለኝና፤ ያለ ፈቃዴ ግን ባደርገው መጋቢነት በአደራ ተሰጥቶኛል።
16For if I announce the glad tidings, I have nothing to boast of; for a necessity is laid upon me; for it is woe to me if I should not announce the glad tidings.
18እንግዲህ ደመወዜ ምንድር ነው? ወንጌልን እየሰበክሁ በወንጌል ካለኝ መብት በሙሉ እንዳልጠቀም ወንጌልን ያለ ዋጋ ብናገር ነው።
17For if I do this voluntarily, I have a reward; but if not of my own will, I am entrusted with an administration.
19ከሰው ሁሉ አርነት የወጣሁ ስሆን የሚበልጡትን እንድጠቅም እንደ ባሪያ ራሴን ለሁሉ አስገዛለሁ።
18What is the reward then that I have? That in announcing the glad tidings I make the glad tidings costless [to others], so as not to have made use, as belonging to me, of my right in [announcing] the glad tidings.
20አይሁድንም እጠቅም ዘንድ ከአይሁድ ጋር እንደ አይሁዳዊ ሆንሁ፤ ከሕግ በታች ያሉትን እጠቅም ዘንድ፥ እኔ ራሴ ከሕግ በታች ሳልሆን፥ ከሕግ በታች ላሉት ከሕግ በታች እንዳለሁ ሆንሁ፤
19For being free from all, I have made myself bondman to all, that I might gain the most [possible].
21ሕግ የሌላቸውን እጠቅም ዘንድ፥ ያለ እግዚአብሔር ህግ ሳልኖር ነገር ግን በክርስቶስ ሕግ በታች ሳለሁ፥ ሕግ ለሌላቸው ሕግ እንደ ሌለኝ ሆንሁ፤
20And I became to the Jews as a Jew, in order that I might gain the Jews: to those under law, as under law, not being myself under law, in order that I might gain those under law:
22ደካሞችን እጠቅም ዘንድ ለደካሞች እንደ ደካማ ሆንሁ፤ በሁሉ መንገድ አንዳንዶችን አድን ዘንድ፥ ከሁሉ ጋር በሁሉ ነገር እንደ እነርሱ ሆንሁ።
21to those without law, as without law, (not as without law to God, but as legitimately subject to Christ,) in order that I might gain [those] without law.
23በወንጌልም ማኅበረተኛ እሆን ዘንድ ስለ ወንጌል ሁሉን አደርጋለሁ።
22I became to the weak, [as] weak, in order that I might gain the weak. To all I have become all things, in order that at all events I might save some.
24በእሽቅድምድም ስፍራ የሚሮጡት፥ ሁሉ እንዲሮጡ ነገር ግን አንዱ ብቻ ዋጋውን እንዲቀበል አታውቁምን? እንዲሁም ታገኙ ዘንድ ሩጡ።
23And I do all things for the sake of the glad tidings, that I may be fellow-partaker with them.
25የሚታገልም ሁሉ በነገር ሁሉ ሰውነቱን ይገዛል፤ እነዚያም የሚጠፋውን አክሊል ሊያገኙ ነው፥ እኛ ግን የማይጠፋውን።
24Know ye not that they who run in [the] race-course run all, but one receives the prize? Thus run in order that ye may obtain.
26ስለዚህ እኔ ያለ አሳብ እንደሚሮጥ ሁሉ እንዲሁ አልሮጥም፥ ነፋስን እንደሚጎስም ሁሉ እንዲሁ አልጋደልም፤
25But every one that contends [for a prize] is temperate in all things: *they* then indeed that they may receive a corruptible crown, but *we* an incorruptible.
27ነገር ግን ለሌሎች ከሰበክሁ በኋላ ራሴ የተጣልሁ እንዳልሆን ሥጋዬን እየጎሰምሁ አስገዛዋለሁ።
26*I* therefore thus run, as not uncertainly; so I combat, as not beating the air.
27But I buffet my body, and lead it captive, lest [after] having preached to others I should be myself rejected.