1ወንድሞች ሆይ፥ ስለ ዘመናትና ስለ ወራት ምንም እንዲጻፍላችሁ አያስፈልጋችሁም፤
1But concerning the times and the seasons, brethren, ye have no need that ye should be written to,
2የጌታ ቀን፥ ሌባ በሌሊት እንደሚመጣ፥ እንዲሁ ይመጣ ዘንድ ራሳችሁ አጥብቃችሁ አውቃችኋልና።
2for ye know perfectly well yourselves, that the day of [the] Lord so comes as a thief by night.
3ሰላምና ደኅንነት ነው ሲሉ ያን ጊዜ ምጥ እርጕዝን እንደሚይዛት ጥፋት በድንገት ይመጣባቸዋል ከቶም አያመልጡም።
3When they may say, Peace and safety, then sudden destruction comes upon them, as travail upon her that is with child; and they shall in no wise escape.
4እናንተ ግን፥ ወንድሞች ሆይ፥ ቀኑ እንደ ሌባ ይደርስባችሁ ዘንድ በጨለማ አይደላችሁም፥
4But *ye*, brethren, are not in darkness, that the day should overtake you as a thief:
5ሁላችሁ የብርሃን ልጆች የቀንም ልጆች ናችሁና። እኛ ከሌሊት ወይም ከጨለማ አይደለንም፤
5for all *ye* are sons of light and sons of day; we are not of night nor of darkness.
6እንግዲያስ እንንቃ በመጠንም እንኑር እንጂ እንደ ሌሎች አናንቀላፋ።
6So then do not let us sleep as the rest do, but let us watch and be sober;
7የሚያንቀላፉ በሌሊት ያንቀላፋሉና፥ የሚሰክሩም በሌሊት ይሰክራሉና፤
7for they that sleep sleep by night, and they that drink drink by night;
8እኛ ግን ከቀን ስለ ሆንን፥ የእምነትንና የፍቅርን ጥሩር የመዳንንም ተስፋ እንደ ራስ ቁር እየለበስን በመጠን እንኑር፤
8but *we* being of [the] day, let us be sober, putting on [the] breastplate of faith and love, and as helmet [the] hope of salvation;
9እግዚአብሔር ለቍጣ አልመረጠንምና፥ በጌታችን በኢየሱስ ክርስቶስ መዳንን ለማግኘት ነው እንጂ።
9because God has not set us for wrath, but for obtaining salvation through our Lord Jesus Christ,
10የምንነቃም ብንሆን፥ የምናንቀላፋም ብንሆን፥ ከእርሱ ጋር አብረን በሕይወት እንኖር ዘንድ ስለ እኛ ሞተ።
10who has died for us, that whether we may be watching or sleep, we may live together with him.
11ስለዚህ እናንተ ደግሞ እንደምታደርጉ፥ እርስ በርሳችሁ ተመካከሩ አንዱም አንዱም ሌላውን ያንጸው።
11Wherefore encourage one another, and build up each one the other, even as also ye do.
12ወንድሞች ሆይ፥ በመካከላችሁ የሚደክሙትን በጌታም የሚገዙአችሁን የሚገሥጹአችሁንም ታውቁ ዘንድ፥ ስለ ሥራቸውም በፍቅር ከመጠን ይልቅ ታከብሩአቸው ዘንድ እንለምናችኋለን። እርስ በርሳችሁ በሰላም ሁኑ።
12But we beg you, brethren, to know those who labour among you, and take the lead among you in [the] Lord, and admonish you,
14ወንድሞች ሆይ፥ እንመክራችኋለን፤ ያለ ሥርዓት የሚሄዱትን ገሥጹአቸው፤ ድፍረት የሌላቸውን አጽኑአቸው፤ ለደካሞች ትጉላቸው፤ ሰውን ሁሉ ታገሡ።
13and to regard them exceedingly in love on account of their work. Be in peace among yourselves.
15ማንም ለሌላው በክፉ ፈንታ ክፉ እንዳይመልስ ተጠንቀቁ፥ ነገር ግን ሁልጊዜ እርስ በርሳችሁ ለሁሉም መልካሙን ለማድረግ ትጉ።
14But we exhort you, brethren, admonish the disorderly, comfort the faint-hearted, sustain the weak, be patient towards all.
16ሁልጊዜ ደስ ይበላችሁ፤
15See that no one render to any evil for evil, but pursue always what is good towards one another and towards all;
17ሳታቋርጡ ጸልዩ፤ በሁሉ አመስግኑ፤ ይህ የእግዚአብሔር ፈቃድ በክርስቶስ ኢየሱስ ወደ እናንተ ነውና።
16rejoice always;
19መንፈስን አታጥፉ፤
17pray unceasingly;
20ትንቢትን አትናቁ፤ ሁሉን ፈትኑ መልካሙንም ያዙ፤
18in everything give thanks, for this is [the] will of God in Christ Jesus towards you;
22ከማናቸውም ዓይነት ክፉ ነገር ራቁ።
19quench not the Spirit;
23የሰላምም አምላክ ራሱ ሁለንተናችሁን ይቀድስ፤ መንፈሳችሁም ነፍሳችሁም ሥጋችሁም ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በመጣ ጊዜ ያለ ነቀፋ ፈጽመው ይጠበቁ።
20do not lightly esteem prophecies;
24የሚጠራችሁ የታመነ ነው፥ እርሱም ደግሞ ያደርገዋል።
21but prove all things, hold fast the right;
25ወንድሞች ሆይ፥ ስለ እኛ ጸልዩ።
22hold aloof from every form of wickedness.
26ከወንድሞች ሁሉ ጋር በተቀደሰ አሳሳም ሰላምታ ተሰጣጡ።
23Now the God of peace himself sanctify you wholly: and your whole spirit, and soul, and body be preserved blameless at the coming of our Lord Jesus Christ.
27ይህ መልእክት ለቅዱሳን ወንድሞች ሁሉ እንዲነበብ በጌታ አምላችኋለሁ።
24He [is] faithful who calls you, who will also perform [it].
28የጌታችን የኢየሱስ ክርስቶስ ጸጋ ከእናንተ ጋር ይሁን፤ አሜን።
25Brethren, pray for us.
26Greet all the brethren with a holy kiss.
27I adjure you by the Lord that the letter be read to all the [holy] brethren.
28The grace of our Lord Jesus Christ [be] with you.